ፓርቲዎች በየመገናኛ ብዙሃኑ የሚያቀርቡት የምርጫ ማኒፌስቶ ለህዝብ ግልፅ በሆነ መልኩ እንዲያቀርቡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅት ህብረት ጠየቀ፡፡
- 5 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 15/2018
ፓርቲዎች በየመገናኛ ብዙሃኑ የሚያቀርቡት የምርጫ ማኒፌስቶ ለህዝብ ግልፅ በሆነ መልኩ እንዲያቀርቡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅት ህብረት ጠየቀ፡፡
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ እስካሁን እየቀረቡ ያሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች የመገናኛ ብዙሃን ክርክር ጠንካራም ደካማ ጎንም አላቸው ብሏል፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች ፖሊሲያቸውን ለህዝቡ ግልጽ ማድረግ እና ባሉት አማራጮች ሁሉ ማግኘት የሚቻል አድርጎ ማስቀመጥ አለባቸውም ተብሏል፡፡

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማድረግ በጣት የሚቆጠር ወር ቢቀረውም በምርጫው ከሚወዳደሩት 47 ፓርቲዎች ክርክር የሚያደርጉትና ፖሊሲያቸውን በግልጽ የሚያስተዋወቁት ጥቂቶቹ ብቻ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ዋና ዳይሬክተር አቶ መስዑድ ገበየሁ ያስረዳሉ።
መራጮች አንድን ፓርቲ የሚመርጡት አስቀድሞ ፖሊሲውን አይተውና በግልጽ መረዳት ሲችሉ ብቻ ነው ብለዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments