ለስኳር በሽታና ለደም ግፊት የሚሆኑ የባህል መድሃኒቶች በዘመናዊ መልኩ ተመርተው ወደ ገበያ ሊቀርቡ ነው ተባለ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
መጋቢት 15/2018
ለስኳር በሽታና ለደም ግፊት የሚሆኑ የባህል መድሃኒቶች በዘመናዊ መልኩ ተመርተው ወደ ገበያ ሊቀርቡ ነው ተባለ፡፡
ከስኳር እና ደም ግፊት ባሻገር የተለያዩ በሽታዎችን ያክማሉ ተብለው የተመረጡ ስምንት የባህል መድሃኒቶች በዘመናዊ መንገድ ተመርተው ለገበያ ሊርቡ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
ምርቶቹ በስፋት በአምራች ኢንዱስትሪዎች ተመርተው ለተጠቃሚ ከመቅረባቸው በፊት ተቆጣጣሪ የመንግስት ተቋማት ተገቢውን ፍተሻ አድርገው ይሁንታ መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡

ይህን ያለው አርማወርሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩ ነው፡፡
እነዚህ የተመረጡ የባህል መድሃኒቶች ከመመረታቸው በፊት ፈዋሽነታቸው እና የጎንዮሽ ጉዳታቸውን በተመለከተ በላብራቶሪ የተላረጋገጡ መሆናቸውን ተነግሯል፡፡
ይህን የነገሩን በአርማወርሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩ የፋርማስቲካል ኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር መሳይ ወ/ማርያም ከባህል መድሃኒት አዋቂዎች ጋር አብረን እየሰራን ነውም ብለዋል፡፡
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

