top of page

ጥቅምት 6 2018 - ''ተገልጋዮችን የሚያንገላቱ፣ ጉቦ የሚቀበሉ ሰራተኞቼን እያባረርሁ በህግ እንዲጠየቁም እያደረግሁ ነው'' ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

  • sheger1021fm
  • Oct 16
  • 1 min read

ተገልጋዮችን የሚያንገላቱ፣ ጉቦ የሚቀበሉ እና መሰል ጥፋቶችን የሚሰሩ ሰራተኞቼን እያባረርሁ በህግ እንዲጠየቁም እያደረግሁ ነው ሲል የከተማዋ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡

 

የነዋሪነት መታወቂያ፣ ያገባና ያላገባ ሰነዶችን ማግኘትና ሌሎች አገልግሎቶችን ለመስጠት ተገልጋዩን የሚያመላልሱ ሰራተኞች መኖራቸው ተነግሯል።

 

እነዚህን ሰራተኞች በስልጠና አግዛለው፤ አጥፍተው የሚገኙትንም መቅጣት እጀምራለሁ ብሏል ተቋሙ።

 

ይህንን ያሉን የኤጀንሲው ምክትል ዳሬክተር ጥጋቡ ሹመይ ናቸው።

 

ree

ነዋሪዎች ከተቋሙ አገልግሎት ፈልገው በሚመጡበት ወቅት፤ ጉዳይ የሚያንዛዙ የተቋሙ ሰራተኞች እንዳሉ ደርሼበታለሁ ማለቱን ሰምተናል፡፡

 

በተለይም እንዲህ ዓይነቱ ችግር በወረዳዎች ላይ እንደሚታይ ነግረውናል፡፡

 

በተያያዘም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ላልሆኑ ሰዎች በሀሰተኛ ሰነድ መታወቂያ የሰጡ የተቋሙ ሰራተኞችን ለህግ በማቅረብ ከስራ በማገድ እና ምንም ዓይነት ማህበራዊ አገልግሎት እንዳያገኙ መደረጉን አስረድተዋል፡፡

 

ችግሩን ለማስተካከል ለተቋሙ ሰራተኞች አስፈላጊውን ስልጠና በመስጠት መፍትሄ እየሰጠን ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡


 ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ማርታ በቀለ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - በሥራቅ አርሲ ዞን ባለንበት በጥቅምት ወር ብቻ 25 ሰዎች መገደላቸውን፣ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ተናገረ።

በኦሮሚያ ክልል በሥራቅ አርሲ ዞን ባለንበት በጥቅምት ወር ብቻ 25 ሰዎች መገደላቸውን፣ ይህንንም የተመለከተው በከባድና ጥልቅ የኃዘን ስሜት መሆኑን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ተናገረ። ቋሚ ሲኖዶስ በኦሮሚያ  ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በጉና፣ በመርቲ፤ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page