top of page

ጥቅምት 6፣2017 - ትናንት ብሔራዊ ባንክ አዲስ መምሪያ ለባንኮች አስተላልፏል፡፡

  • sheger1021fm
  • Oct 16, 2024
  • 1 min read

ትናንት ብሔራዊ ባንክ አዲስ መምሪያ ለባንኮች አስተላልፏል፡፡


የውጭ ምንዛሪ አስተዳደርን የተመለከተው እና በባንኩ መግለጫ የተካተተው ይዘት ከዚህ ቀደም ብሔራዊ ባንክ ለባንኮች ያስተላለፈውን መመሪያ የሚሽር ነው፡፡


የውጭ ምንዛሪ ሲገዙና ሲሸጡ የኮሚሽን እና ተያያዥ ክፍያዎችን ከመግዣና መሸጫ ዋጋ ነጥለው ለብቻ እንዲያሳውቁ ወይም ከደንበኞቻቸው ጋር እንዲደራደሩ የሚል ይዘት አለው፡፡


አዲሱ መመሪያ በተለይ ለአስመጪ ነጋዴዎች ፋይዳው ምን ሊሆን ይችላል? የሚለውን በተመለከተ የምጣኔ ሐብት ባለሞያውን አቶ ዋሲሁን በላይን ጠይቀናቸዋል፡፡


ባለሞያው አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ውሳኔ ለአስመጭዎች ይህ ነው የተባለ ፋይዳ ይኖረዋል ብለው አያምኑም፡፡


ለሰዎች ስነ ልቦና የባንኮች የመግዣና የመሸጫ ዋጋ የቀነሰ መስሎ እንዲታይ ያደርግ ይሆናል እንጂ በስውር ግን ልዩነቱ እንደሰፋ መቀጠሉ አይቀርም ያሉት ባለሞያው ብሔራዊ ባንክ ማድረግ ካለበት ማድረግ የነበረበት ባንኮች ያስከፍሉታል የተባለውን የተጋነነ ኮሚሽን ፈር እንዲይዝ ማድረግ ነበር ሲሉም ነግረውናል፡፡



ትዕግስት ዘሪሁን

Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page