ጥቅምት 4 2018 - ኢትዮጵያ ታሪኳን ሙሉ ከዓለም ፊት ሲያሳንሳት የቆየው አንዱና ዋና ጉዳይ የምግብ ማጣት
- sheger1021fm
- Oct 14
- 1 min read
የሀገሬው ህዝብ ከገበታው ብዙ ጊዜ የሚያገኘው እንጀራ፣ ጤፍን እንኳን የጠገቡት ሀገሮች ረሃብተኞች የሚመገቡት እህል ነው የሚል ተቀጽላ እስከመስጠት የደረሱበት ነው፡፡
"አንደ ኢትዮጵያዊ፣ አንደ ሀገር ስናስበው የፖለቲካ ታሪካችን ያበላሸብን፣ ውጪ ሀገር ስንሄድ አንገታችንን የምንደፋበት፣ የምናዝንበት ጉዳይ ረሃብ በሚባለው ነው፡፡ ጤፍ ምንድነው ሲባል የረሃብተኞች ምግብ ነው ይባላል፡፡ እናንተ እኮ አልተገዛችሁም ግን ረሃብተኛ ናችሁ ይሉናል" ይላሉ የግብርና ተመራማሪው እና መምህሩ ፍሬው መክብብ(ፕ/ር)፡፡
#የምግብ ጉዳይ መልስ ለመስጠት ሀገራት አንዳላቸው አቅም መንገዳቸውም ይለያያል፡፡
ገንዘብ ካለ ምግቡ የትም ይመረት ገዝተው የሚበሉ፣ ዜጎቻቸውን የሚመግቡ ሀገራት ብዙ ናቸው፡፡
የገበሬ ሀገር ባይሆኑም ህዝባቸው የሚመገበው አያጣም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ራሳቸው አምርተው፣ ምርቱንም ተቆጣጥረው የምግብን ጥየቄ ለመመለስ የሚሰሩ አሉ፡፡ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማምጣት፡፡
ለእንደ ኢትዮጵያ ላለ ሀገር ከሌሎች ገዝቶ እንዳይበላ ብዙ የአቅም ችግር፣ አርሶም ፍጆታን ለመሸፈን ባልተቻለበት ሁኔታ የሚበጀው መንገድ በምግብ ራስን መቻል የሚለውን ብቻ መከተል ነው ወይስ በምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ላይ መስራት?
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ንጋቱ ሙሉ












Comments