ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳ ነው የተባለ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና የአፈር የማዳበሪያ ኤክስፖ በኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፈተ።
- 6 hours ago
- 1 min read
ግንቦት 14/2018
ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰናዳ ነው የተባለ ሀገር አቀፍ የሰብል ጥበቃና የአፈር የማዳበሪያ ኤክስፖ በኤግዚቢሽን ማዕከል ተከፈተ።
ኤክስፖው አስመጭዎችን፣ አከፋፋዮችን፣ ተጠቃሚዎችን በቀጥታ የሚያገናኝ እና የገበያ ትስስርን የሚፈጥር ይሆናል ተብሎ ታምኖበታል።
የኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሰብል በሽታ፣ ተባይ፣ የአፈር ለምነት ችግር፣ የቴክኖሎጂ እጥረቶች እና ሌሎች ችግሮችን እያስተናገደ መሆኑ ተነግሯል።

ይህንን ችግር ለመቋቋም የሚያስችል እና ዘርፉ ያሉበትን ችግሮችን ለመፍታት ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቆየው ኤክስፖ የራሱ አስተዋጽኦ ያበረክታል ተብሎ ታምኖበታል።
ዝግጅቱን ዊ ሊንክ የተባለ ድርጅት ከግብርና ሚኒስቴር እና ከሌሎች የመንግስት እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመተባበር እንዳሰናዳው ተነግሯል።
የሰብል በሽታ ክስተት የምርት መቀነስን እያመጣ እና ጫና እያሳደረ መሆኑ ያነሱት የዊ ሊንክ ሀላፊ እንዳለ ገብሬ (ዶ/ር) ዘርፉ ከእንዲህ አይነት ችግር እንዲወጣ ኤክስፖው ያግዛል ብለዋል።
በተጨማሪም ገበሬዎች፣ ፓሊሲ አውጭዎች፣ አስመጭዎች፣ አከፋፋዮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተው ገበሬው እየገጠመው ያለውን ችግር በመለየት እና ከሌሎች የአለም ሀገራት እኩል ቴክኖሎጅን እንዲጠቀም የሚያግዝ የፓናል ውይይት ይደረጋል ተብሏል።
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx





Comments