top of page

ጥቅምት 28፣2016 -በግዙፍ ፕሮጀክቶች ስራ ከተሰማሩ የውጪ ተቋራጮች ልምድ እየተወሰደ አይደለም ተባለ

  • Nov 8, 2023
  • 1 min read

በኢትዮጵያ በግዙፍ ፕሮጀክቶች ስራ ከተሰማሩ የውጪ ተቋራጮች ብዙ ልምድ እየተወሰደ አይደለም ተባለ


ጉዳዩንበህግ ማዕቀፍ መምራት እንደሚያስፈልግ ታምኖበት ይኸው እየተከወነ መሆኑ ተጠቅሷል ።


ጥራትባለው የመሠረት ልማት ኢንቨስትመንት ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ የ2 ቀናት አውደ ጥናት ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል ተጀምሯል ።


የከተማናመሠረተ ልማት ሚኒስቴር ከአለም ባንክ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው በዚሁ መድረክ ላይ ሲነገር እንደሰማነው በኢትዮጵያ አብዛኞቹ ግዙፍ ወይም ሜጋ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ያሉት በውጪ ተቋራጮች ነው ።


ከእነዚህየውጪ ተቋራጮች ማስቀረት የተቻለው ዕውቀት ግን እዚህ ግባ የሚባል እንዳልሆነ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ድኤታ ወንድሙ ሴታ ተናግረዋል ።


ጉዳዩንበህግ ማዕቀፍ መምራት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ይኸው እየተሰራ ነውም ብለዋል ።


የከተማናመሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሣኒ በበኩላቸው በግንባታው ዘርፍ እየታዩ ያሉ የተለያዩ ችግሮች ደካማ መሠረተ ልማት እንዲኖር ምክንያት እየሆነ እንደሚገኝ አመልክተዋል ።


ኢትዮጵያበዘርፉ ያሉ ችግሮችን በደንብ ለይታ የማስተካከያ እርምጃዎች እንድትወስድ ምክር አዘል አስተያየት የሰጡት ደግሞ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ተወካይ ኦስማኔ ዲኦኔ ናቸው ።


ለዚህየዓለም ባንክ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል ።


ባንኩበኢትዮጵያ የተካሄዱ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ከዚህ ቀደምም በገንዘብ ሲደግፍ መቆየቱ ተነግሯል



ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርንወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ሐምሌ 20 2018 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 30.65 ቢሊዮን ዶላር የሚጠይቅ የኃይል ማስፋፊያ ዕቅድ ይፋ አደረገ። እቅዱ የኔትወርክ ማሻሻያ እና ማስፋፊያ፣ የሰብስቴሽን እና ተያያዥ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች፣ ስማርት ግሪድ እና ቆጣሪ ማስፋፋትን እንደሚያካትት አገልግሎቱ ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page