top of page

ጥቅምት 28፣ 2015-በላቲን አሜሪካዋ አገር ፔሩ በሺህዎች የሚቆጠሩ የተቃውሞ ሰልፈኞች ከፖሊስ ጋር መጋጨታቸው ተሰማ



ጥቅምት 28፣ 2015


በላቲን አሜሪካዋ አገር ፔሩ በሺህዎች የሚቆጠሩ የተቃውሞ ሰልፈኞች ከፖሊስ ጋር መጋጨታቸው ተሰማ፡፡


የተቃውሞ ሰልፈኞቹ አደባባይ የወጡት ፕሬዝዳንት ፔድሮ ካስቲሎ ስልጣን እንዲለቁ ለመጠየቅ እንደሆነ ዩሮ ኒውስ ፅፏል፡፡


ፕሬዝዳንት ካስቲሎ ምዝበራ ፈፅመዋል ተብለው እየተዋከቡ መሆኑ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ካስቲሎ ወደ ፕሬዝዳንቱ ሲመጡ በሐብታሞች እና በድሆች መካከል ያለውን የኑሮ ልዩነት ለማጥበብ ቃል በመግባት ነበር ተብሏል፡፡


በአሁኑ ወቅት በፔሩ የደህንነት ምጣኔው በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ይነገራል፡፡


ፕሬዝዳንቱም ስልጣን እንዲለቁ ሕዝባዊ ጫናው እንደበረታባቸው ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


bottom of page