top of page

ጥቅምት 27 2018 - ''በሀይማኖት ሽፋን ግጭት ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን ከድርጊታችሁ ታቀቡ ልንላቸው ይገባል'' የአዲስ አበባ ከተማ የኮሙኒኬሽን ቢሮ

  • sheger1021fm
  • 17 minutes ago
  • 1 min read

በሀይማኖት ሽፋን ስም ግጭት ለመቀስቀስ የሚንቀሳቀሱ አካላትን "ከድርጊታችሁ ታቀቡ" ልንላቸው ይገባል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ቢሮ ተናገረ፡፡


የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የከተማዋ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ከሃይማኖት ሚዲያዎች የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በሰላም ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል።

ree

በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከተማዋ የኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ ሚዲያ ሰላምን ለመስበክ፣ የእርስ በእርስ ግንኙነትን ለማጠናከር ድርሻው ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡


ይሁንና አንዳንድ ግለሰቦች ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ በማህበረሰብ መካከል ግጭት እና ቅራኔ ለመፍጠር እንደሚሰሩ ተናግረው እነዚህን አካላት በቃ ልንላቸው ይገባል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጻሀፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ በበኩላቸው የሃይማኖት ሚዲያዎች በተከታዮቻቸው ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት እንዳላቸው ተናግረው ይህን ቅቡልነት ሰላም ሊያሰፍን፣ መራራቅ ሳይሆን መቀራረብን በሚያመጣ መልኩ ልንጠቀምበት ይገባል ብለዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page