ተማሪዎች በወርቅ ማዕድን ስራ ላይ መሰማራት ለትምህርት ማቋረጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ተናገረ፡፡
- sheger1021fm
- 2 hours ago
- 2 min read
ጥር 21/2018
ተማሪዎች በወርቅ ማዕድን ስራ ላይ መሰማራት ለትምህርት ማቋረጥ አንዱ ምክንያት መሆኑን የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ ተናገረ፡፡
ችግሩን ለመቅረፍ ከፀጥታ አካላትና ከወረዳዎች ጋር በመነጋገር እየሰራ መሆኑን አስረድቷል፡፡
የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ዘነበ በዚህ አመት 315 ሺህ ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዶ 305 ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎችን መዝግበናል ብለዋል፡፡
በክልሉ በየዓመቱ ለተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት አለመምጣትና ከትምህርት ገበታ መቅረት ዋንኛ ምክንያት የማእድን ስራ ተጠቃሽ ነው ብለዋል፡፡
አሁን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከወረዳዎች ጋር በመነጋገር የወርቅን ቁፋሮ ስራ በሚሰራባቸው አካባቢዎች ለትምህርት የደረሰ ልጅ በትምህርት ቀን ስራ እንዳይሰራ ከፀጥታ አካላት ጋር ወረዳዎች ህግ አውጥተው ክትትል እያደረጉ ነው፡፡
ተማሪው ችግር ካለበት በእረፍት ቀናት ብቻ እንዴት ይደረግ የሚለው እየታየ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል፡፡
በክልሉ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ የተማሪ መፅሀፍ እጥረት አለመኖሩን የነገሩን አቶ ምትኩ ዘነበ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ባሉ ክፍሎች በአንዳንድ የትምህርት ዓይነቶች ላይ የመፅሀፍት እጥረት መኖሩን ያስረዳሉ፡፡
የክልሉ መንግስት ችግሩን በማየት በጀት መድቦ ህትመት እንዲደረግ አዟል በቅርቡ ችግሩ ሊፈታ ይችላል ሲሉም አክለዋል፡፡
እንደ እንግሊዘኛ ፣ አካባቢ ሳይንስና በክልሉ ውስጥ በሚሰጡ 5 የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች የሚያስተምሩ የመምህራን እጥረት መኖሩን የቤንሻንጉሉ ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ዘነበ ጠቅሰዋል፡፡
መምህራን ለማፍራት በክልሉ ውስጥ በሚገኘው አንድ የመምህራን ማሰልጠኛ ተቋም ነው፡፡
በዘርፉ መሰማራት የሚፈልጉ ልጆችን መልምለን ክፍተት በታየባቸው የትምህርት ዓይነቶች እጩ መምህራንን እያሰለጠንን ነው ብለዋል፡፡
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማምጣትና የተማሪዎች ማቋረጥን ለመቀነስ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከወረዳዎች ጋር አብሮ እየሰራ ነው ብለዋል አቶ ምትኩ ዘነበ፡፡
የመፅሀፍት እጥረቱ በቅርቡ ይፈታል የሚል እምነት አለኝ የመምህራን እጥረቱ ግን በአንድ ጀንበር መፍታት ስለማይቻል ሰልጣኞች እስከሚመረቁ መጠበቅ ያስፈልጋል ሲሉም መክረዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7












Comments