top of page

ጥቅምት 21 2018 - የሴቶችን ሰላም እና ደህንነት ያስጠብቃል የተባለ ድንጋጌ ኢትዮጵያ ከተቀበለች 25 ዓመት ቢሆንም እስካሁን አላፀደቀችም ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • 6 minutes ago
  • 1 min read

የሴቶችን ሰላም እና ደህንነት ያስጠብቃል የተባለ ድንጋጌ ኢትዮጵያ ከተቀበለች 25 ዓመት ቢሆንም እስካሁን አላፀደቀችም ተባለ፡፡


ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች መካከል አንዱ እንደሆነም ተነግሯል፡፡


ይህንን ድንጋጌ ኢትዮጵያ ብታፀድቅ ሴቶች በተፈጥሮም ይሁን በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚገጥማቸውን ችግር አስቀድሞም ይሁን አደጋው ከደረሰ በኋላ ለመከላከል ይረዳል ተብሏል፡፡


ውሳኔው ወይም አለም አቀፍ ድንጋጌው 13 25 እንደሚባልና ሃገራት ተቀብለው እንዲያጸድቁት ከተላለፈ 25 ዓመት እንደሆነ ሰምተናል፡፡


በሌሎች የዓለም ሀገራት ማፅደቅ ብቻ ሳይሆን በየአምስት ዓመቱ እየተሻሻለ ተግባራዊ እንደሚደረግ የነገሩን የአፍሪካ ሴቶች ሰላምና ደህንነት ኢንስቲትዩት ውስጥ የምርምር ክፍል ሃላፊና ለእዚሁ ተብሎ በተቋቋመ ኮሚቴ ውስጥ ደግሞ የቴክኒክ ኮሚቴ በመሆን ለሁለት ዓመታት ያገለገሉት አቶ ማንይንገረው ሸንቁጥ ናቸው፡፡


ሌሎች 25 ዓመት ሞላው ብለው ለማክበር ቀናት የሚቆጥሩት ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ግን እንዳላፀደቀችው ተናግረዋል፡፡


አሁን ባለው የሰላም እጦት እና ግጭት ለሚቸገሩ ሴቶች እንዲሁም ለሌሎችም ውሳኔ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ኢትዮጵያ እንድታጸድቀው ተጠይቋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድማጥ…

ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page