ጥቅምት 20 2018 - የኮንሶ የእርከን ስራ ላይ አደጋ መደቀኑን፣ ማህበረሰቡም የአኗኗር ዘይቤው በአሉታዊ መልኩ እየተቀየረ መሆኑን ጥናት አሳየ
- sheger1021fm
- 43 minutes ago
- 1 min read
የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውን የኮንሶ የእርከን ስራ ላይ አደጋ መደቀኑን፣ ማህበረሰቡም የአኗኗር ዘይቤው በአሉታዊ መልኩ እየተቀየረ መሆኑን ጥናት አሳየ፡፡
የኮንሶ የድንጋይ እርከኖች በዩኔስኮ መዝገብ የሰፈሩ ማህበረሰቡንም ያስመሰገኑ ሆነው ዓመታት አልፈዋል።
ገደላማውን፣ ፈታኝ ሆነውን መልካም ምድር አካፋና ዶማ ይዘው ባህላዊ እውቀታቸውን ተጠቅመው ለእርሻ ስራ አውለውታል፡፡

ተፈጥሮን ተንከባክበው ከትውልድ ትወልድ አስተላልፈውታል፡፡
በኮንሶ ምድር የሚሰራው የእርከን ስራ፤ ኢትዮጵያም መታወቂያዬ ብላ በዓለም ቅርስነት ካስመዘገበችው 15 ዓመታት ሆኗታል፡፡
ዛሬ ግን እዚያ ድንጋይ እየጠረቡ፣ መሬት እየቆፈሩ የሚሰሩ እጆች፣ የሚያርሱ ወጣቶች በአካባቢ ብዙም አይታዩም፡፡
ወጣቶቹ ፊታቸውን ራቅ ወዳሉ አካባቢዎች ሄደው ማዕድን ወደማውጣት፣ ወደ ንግድ አዙረዋል፡፡
በአካበባዊ በሴቶች ብቻ የሚመሩ ቤተሰቦች መብዛታቸውን፣ተማሪዎች ትምህረት እየተው መምጣታቸውን ጥናቱ አሳይቷል።
የማህበረሰቡ የአኗኗር ዘይቤ እተቀየረ ቅርሱም አደጋ ላይእወደቀ መምጣቱን ጥናት አሳይቷል፡፡
ይህንን ያመጣውም ቀድሞውኑ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚጎዳው የኮንሶ ምድር ዛሬም የዝናብ እጥረት እየተጎዳ በመቀጠሉ ነው፡፡

ይህንን በጥናታቸው ያረጋገጡትና ፎረም ፎርም ሶሻል ስተዲስ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጥናታቸውን ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ትርሲት ሳህለ ድንግል(ዶ/ር) ናቸው፡፡
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s








