top of page

ጥቅምት 20 2018 - በሶስት ወር ውስጥም ከ270 በላይ የመንግስት ተሽከርካሪ ሾፌሮች መቀጣታቸውም ሰምተናል፡፡ 

  • sheger1021fm
  • 38 minutes ago
  • 1 min read

በአዲስ አበባ የመንግስት ወይም 4 ቁጥር የለጠፋ ተሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግ እየተላለፉ አስቸግረውኛል ሲል የከተማዋ ትራፊክ ማኔጅመንት ተናገረ፡፡

 

በሶስት ወር ውስጥም ከ270 በላይ የመንግስት ተሽከርካሪ ሾፌሮች መቀጣታቸውም ሰምተናል፡፡

 

ኮድ 4 መኪና አሽከርካሪዎች የትራፊክ ህግን በመጣስ፣ እንደፈለግን እንሁን ማለታቸው ትራፊክ ህግና ደንብን በማስከበር ስራውን በሚያከናወንበት ጊዜ እንቅፋት እንደሆኑበት ቢሮው አስረድቷል።

 

በአዲስ አበባ ትራፊክ ማነጅመንት የትራፊክ ቁጥጥርና ኩነት አስተዳደር  ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አያሌው ኢቴሳ ህግን ለማስከበር መነሻው ህግ ነው፣ በህግ ፊት ደግሞ ሁሉም እኩል ነው ቢባልም አንዳንድ ባለስልጣናት ግን እንደፈለጉ ባልተፈቀደ መንገድ ያሽከረክራሉ፣ በተቃራኒ መንገድ ይነዳሉ ብለዋል፡፡

 

ለአውቶብስ ብቻ ተብሎ በተሰመረ መስመር ጭምር ማሽከርከር ይመርጣሉ ይህ ድርጊታቸው ደግሞ ለትራፊክ አደጋ መከሰት ጭምር ምክንያት እየሆኑ ነው ብለዋል፡፡

 

አሁን ላይ ህግን ፣የትራፊክ መብራትን በሚጥሱና ባልተፈቀደ መንገድ የሚያሽከረክሩ በለስልጣናትንም ሆነ ማንኛውንም አሽከርካሪ የሚቻለውን እየቀጣን ፣ ጥሶ የሄደውን ታርጋ ቁጥሩን መዝግቦ በመያዝ በሚመለከተው አካል በማስጠራት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ሲሉ አቶ አያሌው ኢቴሳ ነግረውናል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..

 

ገዛ ጌታሁን

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

 
 
 

Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page