top of page

ጥቅምት 14 2018 - የባንክ ደንበኞች ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ ከሰጣቸው ሂሳብ ውጪ በግላቸው ሂሳብ ግብይቶች እንደሚገላበጥ ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Oct 24
  • 1 min read

ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የባንክ ደንበኞች ከሚመለከተው ግብር ሰብሳቢ ከሰጣቸው ሂሳብ ውጪ በግላቸው ሂሳብ የተለያዩ ግብይቶች እንደሚገላበጥ ተሰማ።


ይህን ያረጋገጠው የኢትዮዽያ ብሔራዊ ባንክ ነው።


ባንኩ ባደረግሁት ምርመራ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ግለሰብ ነጋዴዎች በዚህ እንቅስቃሴ እንዳሉ አውቄያለሁ ብሏል።


#የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ባንክ የተለያዩ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰብ ነጋዴዎች የግብር ሰብሳቢ ተቋም ካስመዘገቡት የባንክ ሒሳቦች ውጪ ወደ ግል እና ሶስተኛ ወገን የገንዘብ እንቅስቃሴዎች እየፈፀሙ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።

ree

ይህ አሰራርም ከግብር ሰብሳቢ ባለስልጣናት ቁጥጥር እና ክትትል ለመሸሽ የሚደረግ ተግባር እንደሆነ ባንኩ አስረድቷል።


በተጨማሪም በዚህ መልኩ የሚፈፀሙ የፋይናንስ ግብይቶች እና የገንዘብ እንቅስቃሴዎች የወንጀል ፍሬ ሊሆኑ እንደሚችሉ ባንኩ ከላከልን መግለጫ ተመልክተናል።


እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ ከመርዳት ጋር የተያያዙ ወይም የተገናኙ ሊሆኑ እንደሚችሉም ባንኩ አሳስቧል።


የፋይናንስ ሥርዓቱ ጤናማ እና ታማኝ እንዲሆን አጠቃላይ የኢኮኖሚ ደህንነቱንም ለመጠበቅ ሲባል ብሔራዊ ባንክ ለሁሉም ባንኮች ለንግድና ህገወጥ ድርጊት የሚጠቀሙ ደንበኞች አስመልክቶ መረጃዎችን እያደራጁ እንዲልኩ መመሪያ ማስተላለፋን ሰምተናል።


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page