top of page

ጥቅምት 11 2018 - ባህርዳር እና አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በኒኩለር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ት/ት መስጠት መጀመራቸውን ተናገሩ

  • sheger1021fm
  • 5 minutes ago
  • 1 min read

በኒኩለር ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ትምህርት መስጠት መጀመራቸውን ሁለት ዩኒቨርሲቲዎች ተናገሩ፡፡


ትምህርቱን እየሰጡ ያሉት ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ናቸው፡፡


የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በተያዘው ዓመት ለመጀመርያ ጊዜ በ2ተኛ ዲግሪ ሲያስተምራቸው የነበሩ ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ(ዶ/ር) ነግረውናል፡፡


የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ(ዶ/ር) በበኩላቸው ከሁለተኛ ዲግሪ ባለፈ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅት እያጠናቀቁ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡


በቅርቡ መንግስትበ ኢትዮጵያ የኒኩለር ፕላንት ለሰላማዊ መንገድ እንደሚገነባ የተናገረ ሲሆን ሁለቱ ተቋማት ለዚህ የሚሆን ባለሞያ ለማፍራት ማቀዳቸውንም ጠቅሰዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page