top of page

ጥር 8፣ 2015- በቡርኪናፋሶ ሰሜናዊ ግዛት 50 ያህል ሴቶች በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Jan 16, 2023
  • 1 min read

በቡርኪናፋሶ ሰሜናዊ ግዛት 50 ያህል ሴቶች በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸው ተሰማ፡፡


እገታውን የፈፀሙት ፅንፈኞች እንደሆኑ በብርቱ መጠርጠሩን RNZ ሬዲዮ በድረ ገፁ ፅፏል፡፡


ታጣቂዎቹ የ50 ያህል ሴቶች እገታ የፈፀሙት በሰሜናዊቱ አርቢዳንዳ ከተማ ነው ተብሏል፡፡


አገሪቱ የፅንፈኞች የጥቃት ዒላማ ከሆነች ቆይታለች፡፡


ለቡርኪናፋሶ የፅንፈኞቹ ጉዳይ የተቸገረ ነገር የጠፋ ለመላ እየሆነባት ነው፡፡


በዚሁ ተፅዕኖ ምክንያት 2 ሚሊዮን ያህል ሰዎች ለመፈናቀል እንደተገደዱ ይነገራል፡፡


አገሪቱ በቅርቡ ተደራራቢ ወታደራዊ የመንግስት ግልበጣዎች እንደተካሄዱባት ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች ምርቶች እና አገልግሎቶቻቸውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጋር ለመድረስ እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡

ጥር 14/2018   ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች ምርቶች እና አገልግሎቶቻቸውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጋር ለመድረስ እንደሚቸገሩ ይናገራሉ፡፡   ለዚህም ተስማሚ የሽያጭ ቦታ በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት አለመቻል፣ የበጀት እጥረትን ጨምሮ ሌሎች ችግሮች እንደሚያጋጥሟቸው ይሰማል፡፡   ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች የሚገጥማቸውን ችግር ያቀላል፣ ም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page