top of page

ጥር 6፣ 2015- በሊትዌኒያ በጋዝ ማስተላለፊ አውታር ላይ ፍንዳታ ደረሰ

  • Jan 14, 2023
  • 1 min read

በሊትዌኒያ በጋዝ ማስተላለፊ አውታር ላይ ፍንዳታ ደረሰ፡፡


አውታሩ ወደ ጎረቤት ላቲቪያም ጋዝ የሚያስተላልፍ እንደሆነ ዘ ኒውዚላንድ ሄራልድ ፅፏል፡፡


የማስተላለፊያ አውታሩ እንደፈነዳ ከፍተኛ ቃጠሎ ተቀስቅሶ እንደነበር በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ነበልባሉ ከመሬት እስከ 50 ሜትር ከፍታ ሲወረወር ነበር ተብሏል፡፡


በሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ታውቋል፡፡


በአቅራቢያው ሕንፃዎች የሚኖሩ ሰዎችን ከአደጋ ወደሚጠበቁበት ስፍራ ማውጣት እንደተቻለ ተጠቅሷል፡፡


የጋዝ ማስተላለፊያ ቱቦው በምን ምክንያት ሊፈነዳ እንደቻለ ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም፡፡


በጉዳዩ ላይ ምርመራ ይካሄዳል ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
የሐምሌ 22 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ አሜሪካ እና ሳውዲ አረቢያ ኢራቅ ውስጥ በአፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች ይዞታ ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡ ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ በኢራቅ የሚገኙ አፍቃሪ ኢራን ታጣቂዎች በድሮን ጥቃት አድርሰውብኛል ስትል እንደነበር አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ሳውዲ ጥቃቱን ከማውገዝ በተጨማሪ መበቀሌ አይቀርም በሚል ዝታ ነበር፡፡ በኢራቆቹ አ

 
 
 
የሐምሌ 21 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ጃፓን የጃፓን ደቡባዊ ምዕራብ ክፍል በርዕደ መሬት ተመታ፡፡ ርዕደ መሬቱ የደረሰው ኩማማቶ የተባለው የአገሪቱ ክፍል እንደሆነ ኒኪ እስያ ፅፏል፡፡ የመሬት ነውጡ የተቀሰቀሰው ከምድር በ10 ኪሎ ሜትር ጥልቀት መሆኑ ታውቋል፡፡ ነውጡ በርዕደ መሬት መለኪያ /ሬክተር ስኬል/ 7 ነጥብ 1 ሆኖ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ ቀደም ሲ

 
 
 
የሐምሌ 20 የውጭ ሀገር ወሬዎች

#ቀይ_ባህር በቀይ ባህር የባብኤል መንደብ ወሽመጥ የሚተላለፉ መርከቦች ብዛት በእጅጉ እየቀነሰ ነው ተባለ፡፡ በወሽመጡ የሚተላለፉ መርከቦች ብዛት የቀነሰው የየመን ሁቲዎች ባለፈው ሳምንት የሳውዲ አረቢያን ወደቦች እንከቻችምባታለን ብለው ከዛቱ በኋላ እንደሆነ ሬውተርስ ፅፏል፡፡ ለምሳሌም ትናንት በባብኤል መንደብ የባህ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page