top of page

ጥር 24፣ 2015- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያጋጠማትን ችግር በውይይት ብትፈታው ቤተ ክርስቲያኗም ሀገርም ትጠቀማች ሲሉ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ያጋጠማትን ችግር በውይይት ብትፈታው ቤተ ክርስቲያኗም ሀገርም ትጠቀማች ሲሉ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡


ጉዳዩ ባጋጠመ ማግስት መንግስት የሰጠው ምክር ሰሚ አላገኘም ሲሉም ተደምጠዋል፡፡


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ከሥርዓተ ቤተ-ክርስያቲያን ውጪ ተሰጥቷል ያለችውን የጳጳሳት ሹመት ተከትሎ ጥር 18፣ 2015 ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡


አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው ቅዱስ ሲኖዶስ ሹመቱን የሰጡም የተቀበሉም አባቶች ስልጣነ ክህነታቸው እንዲነሳ እና ከቤተ ክርስቲያን እንዲለዩ ወስኗል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

bottom of page