150 አምራቾችና አገልግሎት አቅራቢዎች የሚሳተፉበት አዲስ ቻምበር ዓለም አቀፍ ንግድ ትርዒት ሊካሄድ ነው፡፡
- Apr 16
- 1 min read
ሚያዝያ 8/2018
150 አምራቾችና አገልግሎት አቅራቢዎች የሚሳተፉበት አዲስ ቻምበር ዓለም አቀፍ ንግድ ትርዒት ሊካሄድ ነው፡፡
የንግድ ትርዒቱ ሲዘጋጅ ለ27 ጊዜ መሆኑን አዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ነግሮናል፡፡
በተለያዩ የቢዝነስ ዘርፎች የተሰማሩ የሀገር ውስጥና የውጪ 150 ተሳታፊዎችን በንግድ ትርኢቱ ምርትና አገልግሎታቸውን ያስተዋውቃሉ፣ ይሸጣሉ ተብሏል፡፡

እንዲሁም የንግድ ለንግድ ግንኙነት ለመጀመር፣ ልምድ ለመቅሰም፣ ለድንበር ተሻጋሪ ሽርክና፣ ለፈጠራ እና ለዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ይገለገሉበታል ተብሎ ተነግሯል፡፡
የንግድ ትርኢቱ መዘጋጀት ንግድ እና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ የበኩሉን አስተዋጾ ያበረክታል ተብሎ አንደታመነበት የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት የኮሙኒኬሽንና አድቮኬሲ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ ምትኩ ነግረውናል፡፡
“ዘላቂ ንግድ፤ የንግድ ተወዳዳሪነት በኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው 27ኛው አዲስ ቻምበር አለም አቀፍ ንግድ ትርዒትን ከሚያዚያ 15 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሶስት ቀናት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ያካሄዳል ተብሏል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments