top of page

ጥር 20፣ 2015- አሜሪካ የጦር መሳሪያ ገበያው ደርቶላታል ተባለ


አሜሪካ የጦር መሳሪያ ገበያው ደርቶላታል ተባለ፡፡


ከወር ገደማ በፊት በተጠናቀቀው ዓመት የአሜሪካ የጦር መሳሪያ ንግድ በ49 በመቶ ማደጉን CGTN ፅፏል፡፡


ዘገባው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ ላይ የተንተራሰ መሆኑ ታውቋል፡፡


ለአሜሪካ የጦር መሳሪያ ገበያ ማደጉ የዩክሬይኑ ጦርነት በዋና ምክንያትነት ቀርቧል፡፡


ንፅፅሩ የተሰራው ከቀዳሚው አመት ጋር ተመሳክሮ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡


አሜሪካ በመንግስት ለመንግስት የመከላከያ ውለታ በአመቱ የ154 ቢሊዮን ዶላር የዋጋ ግምት ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች እንደቸበቸበች ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page