top of page

ጥር 18፣ 2015- በጋምቢያ በመንግስት ግልበጣ ሴራ ተወንጅለው ከነበሩት መካከል አምስቱ በፍርድ ቤት በነፃ ተሰናበቱ


በጋምቢያ በመንግስት ግልበጣ ሴራ ተወንጅለው ከነበሩት መካከል አምስቱ በፍርድ ቤት በነፃ ተሰናበቱ፡፡


በፍርድ ቤት ከክስ ነፃ የተደረጉት ሶስት ወታደሮች እና ሁለት ሲቪሎች እንደሆኑ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


ሌሎች 4 የጦር መኮንኖች ግን በመጪው ሳምንት አዲስ ክስ እንደሚመሰረትባቸው ታውቋል፡፡


ክስ ከሚመሰረትባቸው መካከል የሴራው አቀናባሪ ነው የተባለ መኮንን ይገኝበታል ተብሏል፡፡


በፍርድ ቤቱ ከክስ ነፃ የተደረጉት ሶስት ወታደሮች እና ሁለት ሲቪሎች ከእስር መለቀቃቸው ታውቋል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

bottom of page