top of page

ጥር 18፣ 2015- በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቋረጡን በመቃወም ህዝባዊ ሰልፍ ተደረገ


በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቋረጡን በመቃወም ህዝባዊ ሰልፍ ተደረገ፡፡


በደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቋረጥ ከጀመረ መቆየቱን ዘ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


በአሁኑ ወቅት በየእለቱ እስከ 12 ሰዓታት ለሚደርስ ጊዜ ኤሌክትሪክ እየተቋረጠ ነው ተብሏል፡፡


የጆሃንስበርጉ የተቃውሞ ሰልፍ የተጠራው ዲሞክራቲክ የፖለቲካ ማህበር እንደሆነ ታውቋል፡፡


ሰልፈኞቹ ኤሌክትሪካችንን አታጥፉ፤ መብራታችንን መልሱልን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

bottom of page