top of page

ጥር 18፣ 2015- በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቋረጡን በመቃወም ህዝባዊ ሰልፍ ተደረገ

  • sheger1021fm
  • Jan 26, 2023
  • 1 min read

በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቋረጡን በመቃወም ህዝባዊ ሰልፍ ተደረገ፡፡


በደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ መጥፋት እና መቋረጥ ከጀመረ መቆየቱን ዘ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


በአሁኑ ወቅት በየእለቱ እስከ 12 ሰዓታት ለሚደርስ ጊዜ ኤሌክትሪክ እየተቋረጠ ነው ተብሏል፡፡


የጆሃንስበርጉ የተቃውሞ ሰልፍ የተጠራው ዲሞክራቲክ የፖለቲካ ማህበር እንደሆነ ታውቋል፡፡


ሰልፈኞቹ ኤሌክትሪካችንን አታጥፉ፤ መብራታችንን መልሱልን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page