top of page

ግንቦት 11 2017 - በዓመት ከ7,000 በላይ ሰዎች በኤችአይቪ የሚያዙ ሲሆን አስር ሺህ የሚሆኑ ደግሞ ይሞታሉ የተባለ

  • sheger1021fm
  • 2 days ago
  • 1 min read

በዓመት ከ7,000 በላይ ሰዎች በኤችአይቪ ኤድስ #HIV_AIDS የሚያዙ ሲሆን አስር ሺህ የሚሆኑ ደግሞ ይሞታሉ የተባለ፡፡

 

የስርጭት ምጣኔው ከፍተኛ ሆኖ የታየው በቀን ሰራተኞች በተማሪዎች እና በአጠቃላይ በማህበረሰብ ውስጥ እንዲሆንም ተነግሯል፡፡

 

እንደ ሀገር የስርጭት መጠኑ ከአንድ በመቶ በታች ነው ሲባል ዝቅተኛ ቢመስልም አሁን ባለበት ካልተገታ በድጋሜ ወረርሽኝ የሚባለው በደረጃ ሊደርስ ይችላል ሲሉ በጤና ሚኒስቴር የኤችአይቪኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ ተናግረዋል፡፡

 

በተለይም ደግሞ ወጣቱ ትውልድ ለበሽታ የሚሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ እየሆነ መምጣቱ ወረርሽኝ የመሆን እድሉን ሊያሰፋው ይችላል ሲሉ ስራ አስፈፃሚው አስረድተዋል፡፡

 

በዚህም ከስድስት መቶ ሺህ በላይ ሰዎች ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ እንዳለ እንደሚገመትም ተናግረዋል፡፡

 

የስርጭት መጠኑ ከክልል ክልል ይለያያል ያሉን ስራ አስፈፃሚው አዲስ አበባ መጠኑ ከፍተኛ ሆኖ ከሚታይባቸው መካከል ቀዳሚ እንደሆነችም ያስረዳሉ፡፡

 

ጋምቤላ፣  ሀረሪ፣ ትግራይና አማራ ክልል ከፍተኛ ስርጭት እንደሚታይባቸውም ሰምተናል፡፡

 

እድሜአቸው ከ15 እስከ 29 ዓመት ያሉት ወጣቶች እና ሴቶች አዲስ የመያዝ እድላቸው 70 በመቶ ነው ተብሏል፡፡

 


ማርታ በቀለ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 

 

 

 

Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page