ዶንኪ ድራይቭ የተሰኘ የሜትር አገልግሎት ወደ ስራ መግባቱ ተነገረ።
- sheger1021fm
- 1 hour ago
- 1 min read
ታህሳስ 8/2018
ዶንኪ ድራይቭ የተሰኘ የሜትር አገልግሎት ወደ ስራ መግባቱ ተነገረ።
ሀሴት ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ማህበር ዶንኪ ድራይቭ የተሰኘ አዲስ የትራንስፖርት መተግበሪያ ወይም አፕሊኬሽን ይፋ አድርጓል።
ዶንኪ ድራይቭ የሜትር አገልግሎት ከመንገድ የመጫን አገልግሎትና የዋጋ ድርድር በመተግበሪያው መካተቱ፣ የጉዞ ማስጀመሩ በተሳፋሪው እንዲሆን ማድረግ መቻሉ፣ ያለ ጥሬ ገንዘብ ክፍያን በራሱ መተግበሪያ መፈፀም ማስቻሉና የብድር አገልግሎት ማቅረቡ ልዩ ያደርገዋል ተብሎለታል።
በተጨማሪም በ5 ቋንቋዎች ማለትም በአማርኛ፣ በኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ እንግሊዘኛ እና አረብኛ ቋንቋን ይሰራል ተብሏል።

ዶንኪ ድራይቭ ሰዎችን ማጓጓዝ ብቻ ሳይሆን የዴሊቨሪ ወይንም እቃ ማጓጓዝ አገልግሎትንም ይሰጣልሲባል ሰምተናል፡፡
በሌላ በኩል ወደ ዶንኪ ድራይቭ ተቀላቅለው አገልግሎት ለሚሰጡ አሽከርካሪዎች ካለ ምንም ማስያዣ የብድር አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያደርግ አሰራር መዘርጋቱንም ተነግሯል፡፡
ወደ ስራ ከገባ 6 ወራት ገደማ ያስቆጠረው የኦሮሚያ ባንክ ሚልኪ ታክሲ የፋይናንስ አገልግሎት ከዶንኪ ድራይቭ ጋር በጋራ መስራት መጀመሩን የተናገረው ባንኩ ያለምንም ዋስትና ለአሽከርካሪዎች የብድር አገልግሎቶችን እሰጣለሁ ብሏል።
አሽከርካሪዎቹ ከ5,000 እስከ 50,000 ብር ያለምንም ዋስትና ከኦሮሚያ ባንክ መበደር እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡
ፋሲካ ሙሉወርቅ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








