በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ከትምህርታቸው የራቁ፣ ጎዳና የወጡ ህፃናት ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም መሰናዳቱ ተሰማ፡፡
- sheger1021fm
- 2 hours ago
- 1 min read
ታህሳስ 8/2018
በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ከትምህርታቸው የራቁ፣ ጎዳና የወጡ ህፃናት ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም መሰናዳቱ ተሰማ፡፡
በፕሮግራሙ በሚገኘው ገቢ 50,000 ህፃናት ለመደገፍ ታስቧል፡፡
የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሙን ሜሪጆይ ኢትዮጵያና የሴት ጋዜጠኞች፣ ደራሲያን፣ ምሁራን ጥምረት በጋራ በመሆ እንዳዘጋጁት ተሰምቷል።
አላማውም በችግር ምክንያት ከትምህርት ውጪ የሆኑ ልጆችን ‘’የእኔም ልጆች ናቸው’’ በሚል ልጆቹን ወደ ትምህርት ገበታ ለመመለስ ስራ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ድጋፍ የሚደረግላቸው እና በጥናት የተለዩ በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግር ምክንያቱ የተጎዱ የአማራ፣ የትግራይ፣ የኦሮሚያ፣ የአፋር እና የሶማሌ ክልሎች እንደሆኑ ሰምተናል፡፡
በእነዚ ክልሎች በርካታ ህፃናት በተፈጥሮና በጸጥታ ችግር ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለዋል ሲሉ የነገሩን ለዚሁ ተብሎ በተቋቋመው ጥምረት ውስጥ ሰብሳቢና በሞያቸው ጋዜጠኛ የሆኑት ሮማን ተገኝ ናቸው፡፡
በዚህም መሠረት ከጥር 20 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ በሀገር ውስጥም ይሁን በተለያዩ የዓለም ሀገራት የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እነዚህን በከፋ ችግር ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ህጻናትን ለመርዳት እጆቻችሁን ዘርጉልኝ ሲል ጥምረቱ ጠይቋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1












Comments