top of page

የኢትዮዽያ አየር መንገድ ለመንገደኞቹ በተለይም ለፕሪሚየም ደንበኞቹ 16 ሚሊየን ዶላር የወጣበት እልፍኝ ወይም ላውንጅ ሥራ መጀመሩ ተሰማ።

  • sheger1021fm
  • 1 hour ago
  • 1 min read

ታህሳስ 8/2018


የኢትዮዽያ አየር መንገድ ለመንገደኞቹ በተለይም ለፕሪሚየም ደንበኞቹ 16 ሚሊየን ዶላር የወጣበት እልፍኝ ወይም ላውንጅ ሥራ መጀመሩ ተሰማ።


ለፕሪሚየም መንገደኞቹ የላቀ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል የተባለው ይህ የፕሪሚየም ላውንጅ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ ውስጥ ከሚሰሩ ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ማስፋፍያ አንዱ መሆኑን ሰምተናል።


ይህ በ16 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ለግንባታ ወጭ የተደረገበት ላውንጅ በአውሮፕላን ማረፍያው አገልግሎት እየሰጡ ካሉ ላውንጆች በአቅም እና በያዘው ቦታ ትልቁ ነው ተብሏል።

ree

ልፍኙ በ5,500 ካሬ ቦታ ላይ የተገነባ ሲሆን በአጠቃላይ ሶስት ወለሎችን አካቷል።


የላውንጁክፍሎች ለተለያየ አገልግሎት ታስበው በልዩ ሁኔታ እና በጥንቃቄ የተዘጋጁ ሲሆን በውስጡ የማረፊያ ክፍሎች፣ የስብሰባ አዳራሾች፣ የመዋብያ ክፍሎች፣ የጸሎት እና የጸጥታ ክፍሎች እንዲሁም መታጠቢያ ቤቶችን ጨምሮ በአጠቃላይ 16 የሚሆኑ የተለያዩ አገልግሎት መስጫዎችን ያሟላ ነው።


ይህ እጅግ ዘመናዊ ሆኖ የተገነባው ፕሪሚየም ላውንጅ እስከ 1000 መንገደኞች በአንድ ጊዜ ማስተናገድ ይችላል።


በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያን ከተቀረው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያዎች ጋር ያለውን ተወዳዳሪነት የሚጨምር ነው ተብሏል።


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ከትምህርታቸው የራቁ፣ ጎዳና የወጡ ህፃናት ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም መሰናዳቱ ተሰማ፡፡

ታህሳስ 8/2018   በሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ከትምህርታቸው የራቁ፣ ጎዳና የወጡ ህፃናት ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም መሰናዳቱ ተሰማ፡፡   በፕሮግራሙ በሚገኘው ገቢ 50,000 ህፃናት ለመደገፍ ታስቧል፡፡   የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሙን ሜሪጆይ ኢትዮጵያና የሴት ጋዜጠኞች፣  ደራሲያን፣ ም

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page