ዳሽን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 6.7 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ትርፍ አግኝቻለሁ አለ።
- sheger1021fm
- 2 hours ago
- 1 min read
ታህሳስ 16/2018
ዳሽን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 6.7 ቢሊየን ብር አጠቃላይ ትርፍ አግኝቻለሁ አለ።
አጠቃላይ ሃብቴም ከ254 ቢሊየን ብር ተሻግሯል ብሏል።
የባንኩ ባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል።
በዚሁ ወቅት ሲነገር እንደሰማነው የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ ከ202 ቢሊየን ብር በላይ የደረሰ ሲሆን ካፒታሉም 14 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ሆኗል።

በበጀቱ ዓመቱ 1 ነጥብ 12 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን የጠቀሰው ዳሽን ባንክ አጠቃላይ የብድር ክምችት መጠኑ በሂሳብ ዓመቱ 134 ቢሊየን ብር መድረሱን አክሏል።
አመቱ በአለም አቀፍ ደረጃ ተለዋዋጭ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የታየበት እንደነበር የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ዱላ መኮንን ተናግረዋል።
ዳሽን ባንክ ግን በኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ውስጥ መሪነቱን ያስመሰከበረት ሆኖ አልፏል ብለዋል።
የአገልግሎትና የፋይናንስ ውጤቶቻችን ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ተቋቁመን እያደግን እንደምንገኝ ማሳያዎች ናቸው ያሉት ደግሞ የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው አለሙ ናቸው።
ዳሽን ባንክ አሁን ላይ የደንበኞቹን ቁጥር 7.88 ሚሊየን ማድረሱ የተጠቀሰ ሲሆን የቅርንጫፎቹ ብዛትም 906 ደርሷል ተብሏል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








