የካቲት 9/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
- Feb 16
- 1 min read
የካቲት 9/2018 - የውጪ ሀገራት ወሬዎች
የእስራኤል መንግስት የሀገሪቱ ዜጎች በቀላሉ በዌስት ባንክ መሬት እንዲገዙ የሚያስችል ህግ አፀደቀ።
ህጉ እስራኤላውያን ግለሰቦች በዌስት ባንክ መሬት እንዲገዙ የሚፈቅድ ሲሆን ከገዙት መሬትም የተወሰነውን ለሀገሪቱ የመንግስት አስተዳደር ማስተላለፍ እንደሚችሉ ይደነግጋል።

ህጉ እስራኤል በዌስት ባንክ የምታካሂደውን የአይሁዶች የሰፈራ ፕሮግራም ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ነው በሚል ከተለያዩ ወገኖች ትችት እየቀረበበት ይገኛል።
የአውሮፓ ህብረት አባላት እና የአረብ ሀገራት ትችቱን ከሰነዘሩት መካከል እንደሆኑ DPA international ዘግቧል።
የእስራኤል መንግስት ግን ህጉ የዜጎችን ሃብት የማፍራት መብት ታሳቢ አድርጎ ብቻ የተዘጋጀ ነው ብሏል።
የሡዳን ጦር በምዕራብ ኮርዶፋን የነበረን የፈጥኖ ደራሹ ሃይልን የአየር ሃይል ማዘዣ ሰፈር አወደምኩ አለ።
በጦር ሰፈሩ በነበሩ የፈጥኖ ደራሹ ሃይል ተዋጊዎች እና የጦር መሳሪያ ክምችት ላይ ከበድ ያለ ጉዳት ማድረሱን ጠቅሷል።
ከዚህ በላይ ግን የሰጠው ዝርዝር መረጃ እንደሌለ አናዱሉ ፅፏል።
የሡዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል በጄኔራል አልቡርሃን በሚመራው የሀገሪቱ ጦር ደርሶበታል ስለ ተባለው ጥቃት ያለው ነገር የለም።
በጀኔራል አልቡርሃን የሚታዘዘው የሡዳን ጦር እና ጀኔራል ሃምዳን ዳጋሎ የሚመሩት ፈጥኖ ደራሽ ሃይል አሁን ላይ በዳርፉር እንዲሁም ሰሜን ፤ ደቡብ እና ምዕራብ ኮርዶፋን ከባድ ውጊያ እያካሄዱ እንደሚገኙ ተነግሯል።
ሶስት ዓመት ባስቆጠረው የሁለቱ ሃይሎች ውጊያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የሡዳን ዜጎች መገደላቸው የተነገረ ሲሆን 13 ሚሊየን ያህሉ ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ተብሏል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments