የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ "ጉዞ ወደ FIFA የዓለም ዋንጫ 2026"በሚል ሲያካሂድ በነበረው የሽልማት መርሐ ግብር አሸናፊ የሆኑትን ሁለት እድለኞች ይፋ አደረገ።
- 8 hours ago
- 1 min read
ሚያዝያ 17/2018
የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ "ጉዞ ወደ FIFA የዓለም ዋንጫ 2026"በሚል ሲያካሂድ በነበረው የሽልማት መርሐ ግብር አሸናፊ የሆኑትን ሁለት እድለኞች ይፋ አደረገ።
ባንኩ ከቪዛ ካርድ ጋር በመሆን የቪዛ ካርዶቹን ለሚጠቀሙ ደንበኞቹ በሰሜን አሜሪካ ለሚካሄደው የዘንድሮ የአለም ዋንጫ ሁለት ባለዕድለኞች ጉዞ ሙሉ ወጪያቸውን እንደሚሸፍን መናገሩ ይታወሳል።

ሁለቱ አሸናፊዎችን ለማወቅ መርሃግብሩ ሲካሄድ የቆየው ከመጋቢት 12 እስከ ሚያዚያ 16/2018 ድረስ ነው።
ዛሬ በወጣው ሽልማት ተሳታፊ ለመሆን ባንኩ በቅርቡ ወደ ሥራ ያስገባቸው ሶስት የካርድ አገልግሎቶች፣ በሀገር ውስጥ POS ማሽኖች ላይ ከብር 200 ባላይ ከፍያዎች የፈጸሙ፣ በባንኩ ATM ብር 1000 እና ከዛ በላይ ገንዘብ ያስገቡ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ከ20 ዶላር በላይ ክፍያ የፈጸሙ ደንበኞችን በዕጩነት አቅርቦ በዋናው መሥሪያ ቤት ባካሄደው የዕጣ ማውጣት ስነስርዓት ሁለት ዕድለኞችን ለይቷል።
በዚህም ነፃነት አሰፋ እና አልዓዛር ንጉሱ የተባሉ ደንበኞች እጣው ወጥቶላቸዋል።
በተለያየ ምክንያት እጣ የወጣላቸው ሰዎች ጉዟቸው ባይሳካ በሚል ሌሎች ሁለት እጣ ወጥቶላቸዋል።
የዚህ ሽልማት ባለ እድለኞች ተጨማሪ አንድ አንድ ሰው ይዘው ወደ አለም ዋንጫው ይጓዛሉ፣የቪዛ ጉዳያቸውን፣ሙሉ ወጪያቸውን የሚጨርስላቸውም ባንኩ መሆኑ ተጠቅሷል።
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments