top of page

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገበት መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • 22 hours ago
  • 1 min read

ጥቅምት 26 2018

 

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥርዓተ ትምህርት ክለሳ እየተደረገበት መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

 

‌‎የሚከለሰው ሥርዓተ ትምህርትም በ2018 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርስቲ የገቡ ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

 

በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ተልዕኮ መሰረት ባደረገ መልኩ ስርዓተ ትምህርቱን የመከለስ ስራ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

 

ree

ክለሳው ያስፈለገው የቀድሞዎቹ ሥርዓተ ትምህርቶች ዘመኑን ያልዋጁና ከ21ኛው ክፍለ ዘመን ጋር በአግባቡ ያልተቃኙ በመሆናቸው ነው ብለዋል።

 

‎አዲሱ እየተከለሰ ነው የተባለው የከፍተኛ ትምህርት፣ ሥርዓተ ትምህርት ተመራቂዎች በትምህርት ፕሮግራሞቹ ከተማሩ በኋላ ሊኖራቸው የሚገባውን እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት በአግባቡ የፈተሸ መሆኑን መሪ ሥራ አስፈጻሚው አስረድተዋል፡፡

 

በትምህርት ሚኒስቴር የሥርዓተ ትምህርት ፕሮግራሞች ዴስክ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ነገዎ በበኩላቸው የሚከለሰው ሥርዓተ ትምህርት ሙያና ተግባር ተኮር መሆኑን ጠቅሰው ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ምሩቃንን ማፍራት እንደሚያስችል ተናግረዋል።‎

 

በሁለት ዙሮች እስካሁን 55 የትምህርት ፕሮግራሞች መከለሳቸውን አንስተው እስከ ዓመቱ መጨረሻም ከ80 የሚበልጡ ፕሮግራሞች እንደሚከለሱ ጠቅሰዋል፡፡

 

አዲስ የተከለሱት የትምህርት ፕሮግራሞች በ2018 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርስቲ የገቡ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ወይም ከመጭው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረጉም ተጠቅሷል።

 

በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page