የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዚህ በኋላ ኢንዱስትሪዎች የሚገነባባቸው አካባቢዎች መሰረተ ልማት ለሟሟላት አመቺ ካልሆነ አይገነባም አለ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
የካቲት 13/2018
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዚህ በኋላ ኢንዱስትሪዎች የሚገነባባቸው አካባቢዎች መሰረተ ልማት ለሟሟላት አመቺ ካልሆነ አይገነባም አለ፡፡
አሁን ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት በማሰብ መሬት በአንዳንድ ክልሎች ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው ብሏል፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች ከዚህ ቀደም ከተዘጉ ኢንዱስትሪዎች መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ስራ ለመመለስ ተችሏል ብሏል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት የውጪ ምንዛሪ በተፈለገው ልክ አለማግኘትና ሌሎችም ችግሮች በተለያዩ ጊዜያት በአምራቾች ዘንድ ሲነሳ የነበረ ችግር ነው ብለዋል፡፡
መንግስት እነዚህ ችግሮችን ለመፍታት ባለፉት 4 ዓመታት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ባለፉት 3 አማታት የተካሄደው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከመጀመሩ በፊት የኢንደስትሪዎች የማምረት አቅም 46 ከመቶ ነበር አሁን ወደ 66 ከመቶ ማደጉን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡
ችግሮች አሁንም ድረስ በዘርፉ አሉ ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጦች እየታየ ነው ይላሉ፡፡
ከዚህ ቀደም የነበረው የዘርፉ ፖሊሲ ሁሉንም ባለሃብቶች እኩል ነበር የሚመለከታቸው የተሻሻለው ፖሊሲ ግን ለሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል ሚኒስትሩ አቶ መላኩ፡፡
ነገር ግን አሁንም ብዙ ድጋፎች ማድረግ ይጠበቅብናል ያሉት ሚኒስትሩ መንግስት ዘርፉን በተመለከተ በየጊዜው የሚያወጣቸው ፖሊሲዎችና እስትራቴጂዎች ለኢትዮጵያውያን አምራቾችን ትኩረት የሰጠ ነው፡፡
ከዚህ ቀደም እያመረቱ የነበሩና አሁን ያለውን ቴክኖሎጂ የማይጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ከገብያው እየወጡ ነው ይህ ሚሆነው መወዳደር ስለማይችሉ ነው ብለዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7








