top of page

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዚህ በኋላ ኢንዱስትሪዎች የሚገነባባቸው አካባቢዎች መሰረተ ልማት ለሟሟላት አመቺ ካልሆነ አይገነባም አለ፡፡

  • 2 hours ago
  • 1 min read

የካቲት 13/2018 

 

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዚህ በኋላ ኢንዱስትሪዎች የሚገነባባቸው አካባቢዎች መሰረተ ልማት ለሟሟላት አመቺ ካልሆነ አይገነባም አለ፡፡

 

አሁን ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋት በማሰብ መሬት በአንዳንድ ክልሎች ለማዘጋጀት እየተሰራ ነው ብሏል፡፡

 

በተለያዩ ምክንያቶች ከዚህ ቀደም ከተዘጉ ኢንዱስትሪዎች መካከል አብዛኛዎቹ ወደ ስራ ለመመለስ ተችሏል ብሏል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የፋይናንስ አቅርቦት እጥረት የውጪ ምንዛሪ በተፈለገው ልክ አለማግኘትና ሌሎችም ችግሮች በተለያዩ ጊዜያት በአምራቾች ዘንድ ሲነሳ የነበረ ችግር ነው ብለዋል፡፡

 

መንግስት እነዚህ ችግሮችን ለመፍታት ባለፉት 4 ዓመታት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

 

ባለፉት 3 አማታት የተካሄደው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከመጀመሩ በፊት የኢንደስትሪዎች የማምረት አቅም 46 ከመቶ ነበር አሁን ወደ 66 ከመቶ ማደጉን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡

 

ችግሮች አሁንም ድረስ በዘርፉ አሉ ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጦች እየታየ ነው ይላሉ፡፡

 

ከዚህ ቀደም የነበረው የዘርፉ ፖሊሲ ሁሉንም ባለሃብቶች እኩል ነበር የሚመለከታቸው የተሻሻለው ፖሊሲ ግን ለሀገር ውስጥ ባለሃብቶች የበለጠ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል ብለዋል ሚኒስትሩ አቶ መላኩ፡፡

 

ነገር ግን አሁንም ብዙ ድጋፎች ማድረግ ይጠበቅብናል ያሉት ሚኒስትሩ መንግስት ዘርፉን በተመለከተ በየጊዜው የሚያወጣቸው ፖሊሲዎችና እስትራቴጂዎች ለኢትዮጵያውያን አምራቾችን ትኩረት የሰጠ ነው፡፡

 

ከዚህ ቀደም እያመረቱ የነበሩና አሁን ያለውን ቴክኖሎጂ የማይጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ከገብያው እየወጡ ነው ይህ ሚሆነው መወዳደር ስለማይችሉ ነው ብለዋል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

 

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page