የኢትዮጵያዊያን የቆየ የጋራ አብሮነት እሴቶች እንደ ቡና መጠራራት፣ እድርና ማህበር ያሉ ማህበራዊ ትስስሮች ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ተባለ።
- 8 minutes ago
- 1 min read
መጋቢት 16/2018
የኢትዮጵያዊያን የቆየ የጋራ አብሮነት እሴቶች እንደ ቡና መጠራራት፣ እድርና ማህበር ያሉ ማህበራዊ ትስስሮች ወንጀልን በመከላከል ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው ተባለ።
እነዚህ ማህበራዊ ቅርርቦሾች በሚላሉበት ወቅት ደግሞ ወንጀል በተደጋጋሚ የመከሰት ዕድሉ ሰፊ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስነ-ወንጀል የስነ ልቦና መምህሩ ዋና ኢንስፔክተር ጉግሳ ገብረግዚአብሔር አንድ ማህበረሰብ ጠንካራ የጋራ እሴቶች ሲኖሩት ወንጀልን የመቆጣጠር አቅሙ ይጨምራል ብለዋል።
በአንድ አካባቢ የሚኖር ማህበረሰብ ወንጀል እንዳይፈጠር፣ ስርቆት እንዳይኖር፣ ግድያን እንዳይከሰት፣ ከማህበረሰቡ እሳቤ ያፈነገጠ ባህሪም እንዳይኖር የሚቆጣጠርበት ስልት ማህበራዊ ቅርርቦሹን ማጠናከር ነው የሚሉት ወ/ኢ/ር ጉግሳ ቡና ተጠራርቶ በጋራ መጠጣት፣ ማህበርና እድር ደግሞ የማህበረሰቡን መቀራረብና አብሮነት እንደሚያድጉ ተናግረዋል።
ዓይነቱ ዘዴ በአብዛኛው በገጠሪቱ አካባቢ ጥቅም ላይ እንደሚውልም ዋ/ኢሩ አስታውሰዋል፡፡
በተጨማሪም ያጠፋ የሚቀጣበት፣ ተበዳይ የሚካስበት ባህላዊ የሽምግልና ሥርዓት መቅረት የሌለበት ወንጀልን ለመቀነስ ዓይነተኛ መሳሪያ እንደሆነም የስነ ወንጅል አስተማሪው መክረዋል፡፡
ወንጀልን ለመቆጣጠር በቴክኖሎጂና በፖሊስ ብቻ እንደማይሆን የጠቀሱት አስተማሪው ማህበረሰባዊ ግንኙነቶችን ማጠናከር ፣ ጎረቤት ለጎረቤት መጠባበቅና የቆዩ ባህላዊ እሴቶችን ለዘመኑ ወንጀል መከላከያ ስልት እንዲሆኑ አላምዶ መጠቀም ዋነኛው መፍትሄ መሆኑን ዋና ኢንስፔክተር ጉግሳ ገብረግዚአብሔር አሳስበዋል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ገዛ ጌታሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

