የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ሼባ ማይልስ እና አኮያ ፕሮፐርቲስ አብሮ ለመስራት ስምምነት መፈራረማቸው ተሰማ።
- sheger1021fm
- 13 minutes ago
- 1 min read
ታህሳስ 8/2018
የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ሼባ ማይልስ እና አኮያ ፕሮፐርቲስ አብሮ ለመስራት ስምምነት መፈራረማቸው ተሰማ።
በስምምነቱ መሰረት ከአኮያ ፕሮፐርቲስ መኖሪያ ቤቶችን እና የንግድ ሱቆችን የሚገዙ ደንበኞች፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሼባ ማይልስ የጎልድ አባልነት ሽልማት በክብር እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።
ይህም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ እና የሪል ስቴት ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ አንደታመነበት ከተላከልን መግለጫ ላይ ተጠቅሷል፡፡

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ሼባ ማይልስ ጋር አብሮ ለመስራት መፈራረሙ የተነገረው አኮያ ፕሮፐርቲስ በሪል ስቴት፣በቡና ምርትና ኤክስፖርት እንዲሁም በተሽከርካሪ ግብይት የተሰማራ አና ከ230 በላይ ሰዎች የስራ እድል የፈጠረ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ኩባንያው ተዋናይ እፀህይወት አበበን የድርጅቱ የብራንድ አምባሳደር ማድረጉንም ሰምተናል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








