top of page

የአፍሪካ ቀን

  • 46 minutes ago
  • 2 min read

ግንቦት 18/2018

 

አፍሪካ በምዕራባውያን ሚዲያ የግጭትና የረሃብ ቀጠና ተደርጋ በመሳሏ ምክንያት ለኢንቨስትመት አመቺ ካልሆኑ አህጉራት መካከል በመሆኗ በየዓመቱ 4.2ቢሊዮን ዶላር እንደምታጣ ጥናት አሳየ፡፡ 


በየዓመቱ ግንቦት 17 የአፍሪካ ቀን የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት) እ.ኤ.አ በ1963 በዚህ ቀን መመስረቱን ተከትሎ የአፍሪካ ቀን ተብሎ ይከበራል።


የዘንድሮውን  የአፍሪካ ቀን Africa no filter የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት "አፍሪካ እየጠበቀች አይደለም"የሚል የሚዲያ ዘመቻ በማስጀመር 63ኛውን የአፍሪካ ቀን በትላንትናው እለት አክብሯል፡፡


አፍሪካ በምዕራባውያን ሚዲያ ለዘመናት የረሃብና የሰቆቃ ምልክት ተደርጋ ስትገለፅ ቆይታለች ያሉን የአፍሪካ ኖ ፊልተር ዋና ዳይሬክተር ሞኪ ማኩራ ናቸው፡፡


ድርጅታቸው  አፍሪካ የተጣለባትን የጠለሸ ስም በትክክለኛ  መልኳ ለመከየር እንደሚሰራና ላለፉት 6 ዓመታት የውትወታና የጥናትና ምርምር ስራዎችን ሲሰራ እንደነበር ዳይሬክተሯ  ነግረውናል፡፡


ዋና ዳይሬክተሯ ሞኪ ማኩራ እንደሚሉት Africa no filter ባደገው ጥናት አፍሪካ ምዕራባውያን በሚዘውሯቸው ሚዲያዎች በተሰጣት ስም ምክንያት ለኢንቨስትመት ከማይመረጡ አህጉራት ቀዳሚዋ ሆናለች፤በዚህም ምክንያት በየዓመቱ 4.2 ቢሊዮን ዶላር እያጣች ነው ብለውናል፡፡


"አፍሪካ እየጠበቀች አይደለም" የተሰኘውና በትላንትናው እለት የተጀመረው የሚዲያ ዘመቻ አፍሪካ ማንንም ሳትጠብቅ፤የምንም ልገሳ ሳያስፈልጋት በራሷ መቆም የምትችል አህጉር እንደሆነችና እስካሁን ስለ አፍሪካ ሲነገር የቆየው ትክክለኛ ማንነቷ አለመሆኑን ለማሳየት ያለመ ነው ተብሏል፡፡


ዘመቻው ለ3ዓመታት የሚቆይ ሲሆን በየወሩ በ25ተኛው ቀን የሚቀጥል፤በተለይ ወጣቶች በያዙት የሚዲያ አማራጭ አሁን ያለውን የአፍሪካ ትክክለኛ ገጽታ እንዲያሳዩ ድርጅቱ አፍሪካ ኖፊለተር በገንዘብና በሃሳብ እንደሚደግፋቸው ዋና ዳይሬክተሯ ሞኪ ማኩራ ነግራናል፡፡  


በጌትስ ፋውንዴሽን የገንዘብ ድጋፍ ይህንን ስራ እንደተ ጀመረ የነገሩን ሃላፊዋ ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት በየወሩ የሚሰራው አስተሳሰብን የማስቀየር ስራ በመላው አፍሪካ የሚሰራ መሆንና በተለይ እንደ ፊልም ባሉ የኪነጥበብ ስራዎችም መልዕክቶቹ እንደሚስተጋቡ ተናግረዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ……


ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…











 

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ……

 

 

ምንታምር ፀጋው

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page