አንዳንድ ሆቴሎች ከመደበኛው ክፍያ በተጨማሪ የአገልግሎት በሚል የሚያስከፍሉት ክፍያ!
- 20 minutes ago
- 1 min read
ግንቦት 18/2018
በአዲስ አበባ የምግብና መጠጥ አገልግሎት የሚሰጡ አንዳንድ ሆቴሎች ከመደበኛው ክፍያ በተጨማሪ የአገልግሎት እያሉ ሂሳብ ይቀበላሉ።
በሌሎች ሀገራት ደንበኛው በተሰጠኝ አገልግሎት ተደስቻለሁ ካለ ብቻ በራሱ ፍቃድ የሚፈጽመው የአገልግሎት ክፍያ (ቲፕ)በእነዚህ ሆቴሎች አስገዳጅ ሆኖ እየተጠየቀ ነው።
በዚህ መልክ የተሰበሰበውን ገንዘብ በመስተንግዶ ስራ ላይ ለተሰማሩ ሠራተኞቻቸው እንደሚያከፋፍሉትም የሆቴሎቹ ባለቤቶችና ሃላፊዎች ሲናገሩ ይሰማል።
በርግጥ ግን የአገልግሎት ክፍያ ወይም ቲፕ በአስገዳጅነት ሊጠየቅ ይችላል? ሆቴሎቹ እንዳሉት ለአስተናጋጆቹ ስለ ማከፋፈላቸውስ እንዴት ይረጋገጣል?
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ……
ማርታ በቀለ

