top of page

የአፈርን ለምነትና ጤናማነት በመጨመር የተሻለ ምርት እንዲገኝ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎች ስራ ላይ እየዋሉ ነው ተባለ ፡፡

  • 33 minutes ago
  • 1 min read

የካቲት 11/2018  

 

የአፈርን ለምነትና ጤናማነት በመጨመር የተሻለ ምርት እንዲገኝ የሚያግዙ ቴክኖሎጂዎች ስራ ላይ እየዋሉ ነው ተባለ ፡፡

 

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ግብርናና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ እየተተገበረ ያለው ይህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እየተራቆተ እና ምርት እየራቀው የመጣውን ለግብርና የሚውል መሬት ለምነት ለመመለስ ያግዛል ተብሏል፡፡

 

ይህ ባዮቻር የተባለው ቴክኖሎጂ እየተራቆተ የመጣውን የእርሻ መሬት ለማከም እንደሚረዳ የነገሩን በጅማ ዩንቨርስቲ ግብርናና የእንስሳት ህክምና ኮሌጅ ውስጥ መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም የአፈር ለምነት ለማስጠበቅ የተለያዩ ጥናቶችን ያደረጉት ዶ/ር ሚልክያስ አህመድ ናቸው፡፡

 

የእርሻ መሬት ከጊዜ ወደ ጊዜ የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም እንኳን የሚፈልገውን ያክል ምርት መስጠት እየቻለ አይደለም የሚሉት ዶ/ር ሚልክያስ ይህ ዓይነቱ ቴክኖሎጂ የተሻለ ምርት ለማግኘት ያግዛል ብለዋል፡፡

 

ይህንን ምክንያት በማድረግ ሃገር በቀል መፍትሄዎች በሀገሬው ልጆች መስጠት አስፈላጊ በመሆኑ በአካባቢ ከሚገኙ ተረፈ ምርቶች ባዮቻርን በማዘጋጀት ለአካባቢው አርሶ አደሮች እየተሰጠ እንደሆነም ነግውናል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

 

ማርታ በቀለ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page