top of page

የቡና ዓይነቶች ጣዕም፣ የቀለም እና የዋጋ ልዩነታቸው ታዲያ ከየት መጣ?

  • 12 minutes ago
  • 2 min read

የካቲት 11/2018  

 

ኢትዮጵያ የከፋ፣ የጅማ፣ የሀረር እና ይርጋ ጨፌ የቡና ዝርያዎች መገኛ ሀገር ናት፡፡

 

እነዚህ የቡና ዓይነቶች መነሻቸው አንድ ፤ ዝርያቸውም ተመሳሳይ፣ መሆኑን የዘርፉ ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡

 

የጣዕም፣ የቀለም እና የዋጋ ልዩነታቸው ታዲያ ከየት መጣ?

 

ተመራማሪዎች በማስረጃ፣ የታሪክ ምሁራን በቅርስ፣ አርኪ ኦሎጂስቶችም በመሬት ውስጥ ምስክርነት ሌላውም ሌላውም  አለኝ ያለውን ማስረጃ በማቅረብ ኢትዮጵያ ቡናን ለአለም ያስተዋወቀች ምድር ስለመሆኗ  ይሞግታሉ። 

 

የቡና ርስት ኢትዮጵያ ስለመሆኗ ሳይንስም፣ ታሪክም፣ ቢያረጋግጥም፣  መጠሪያው 'ኮፊ አረቢካ' መሰኘቱን ብዙዎች በቁጭት ይናገሩታል፡፡

 

“ኮፊ አረቢካ” የሚለዉን ስያሜ ያገኘው የቀደምት የአረብ ነጋዴዎች ከኢትዮጵያ ወስደው በራሳቸው ስም ሰጥተው መጠሪያው እንዳደረጉት ታሪክ ጠቅሰው ፣ ማስረጃ አቅረበው የሚናገሩ አሉ፡፡

 

ያም ሆነ ይህ የቡና እትብት የኢትጵያ ምድር ስለመሆኑ እርግጥ ነው ይላሉ ለ37 ዓመት ጥናት ያደረጉት አቶ ሰለሞን ተክሌ።

 

የታሪክ አስተማሪው አቶ አሰፋ ገብረማሪም ደግሞ ኢትዮጵያዊነትና ቡና የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው።

 

ቡና በኢትዮጵያዊን ማህበራዊ ህይወት ውስጥ ያለው ፋይዳ ከኢኮኖሚያዊ ጥቅሙ በላይ ገዝፎ ይታያል ይላሉ፡፡

 

በቡና መገኛዋ  ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ የጅማ፣ የሐረር፣ የከፋ፣ የይርጋ ጨፌ ሌላም ሌላም መጠሪያ ይዘው የሚታወቁት የቡና ዓይነቶች ፣ ስለምን በጣዕም፣ በቀለምና በዋጋ መለያየት ከአፈሩ ፣ ከሚደረግለት እንክብካቤ፣ ከአየር ፀባዩና በሌሎች ምክንያት እንደሆነ ተመራማሪው  ሰለሞን ተክሌን ይጠቁማሉ፡፡

 

ቡና የኢትዮጵያ ለዓለም የሰጠችው ስጦታ ነው።

 

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ኑሯቸው ከቡና ጋር በቀጥታ የተቆራኘ ነው።

 

የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ በማስገኘትም የቡና ስም ጎልቶ ይጠራል፡፡

 

ቡና ዝርያው አንድ ቢሆንም፣ ምድሪቱ በቸርነቷ ያደለችው የተለያየ መዓዛ ግን ለዓለም ገበያ ልዩ ድምቀት ሆኗል።

 

ዛሬም ድረስ በየቤቱ የሚጤሰው የቡና ጪስ የፍቅር፣ የአንድነትና የጽናት ምልክት ሆኖ ቀጥሏል።

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

 

ገዛ ጌታሁን

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page