top of page

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክን የኃይል አቅርቦት ሳይቆራረጥ እንዲያገኝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ መስራቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • 2 hours ago
  • 1 min read

ጥር 25/2018


የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክን የኃይል አቅርቦት ሳይቆራረጥ እንዲያገኝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል መስመር ዝርጋታ መስራቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናገረ፡፡


የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከዚህ በፊት የራሱ ብቸኛ መስመር ስላልነበረው የኃይል መቆራረጥና መዋዠቅ ያጋጥመው ነበር ተብሏል፡፡


አሁን ላይ ከአዳማ ቁጥር 3 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቀጥታ አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት መካከለኛ መስመሮች ለፓርኩ መዘርጋቱን አገልግሎቱ አስረድቷል፡፡


ማከፋፋያ ጣቢያው 40 ሜጋ ዋት ኃይል ለፓርኩ በቀጥታ ማቅረብ የሚያስችል ዓቅም ያለው ሲሆን፤ አምራች ኢንዱስትሪዎቹ አሁን የሚጠቀሙትን የኃይል መጠን ያሳድገዋልም ተብሏል፡፡


አሁን ላይ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ እያደገ እና ኢንዱስትሪዎች እየሰፉ መሄዳቸውን ተከትሎ ዘላቂ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል ብሏል፡፡


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እነዚህን ፍላጎቶች በፍጥነት፣ በፈጠራ እና በቅልጥፍና ለማሟላት እየሰራ እንደሚገኝ በላከልን መግለጫ ላይ ጠቅሷል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page