የአ/አ ት/ት ቢሮ ከት/ቤቶች ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ለወላጆች ቅሬታ ፈጥሯል
- sheger1021fm
- 3 hours ago
- 1 min read
ህዳር 24 2018
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከመንግስትና የግል ትምህርት ቤቶች ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት ለወላጆችና መምህራን ቅሬታ ፈጥሯል፡፡
ቢሮው ከ256 ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 40,000 ተማሪዎች በ54 ማዕከላት በተሻለ የማስተማር ችሎታቸው በተመረጡ መምህራን ከመደበኛው የትምህርት ቀን ወጪ የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠሁ ነው ብሎ ነበር፡፡
እንዲህ ዓይነቱ አሰራር በሌሎች ሀገራትም የተለመደ ቢሆንም ከተማሪ ወላጆችና መምህራን በማጠናከሪያው ላልተካተቱ ተማሪዎችስ ምን ታስቧል? የሚል ጥያቄ አስነስቷል፡፡
የተማሪ ወላጆችና መምህራን ጥሩ ውጤት ላላቸው ተማሪዎች ማጠናከሪያ ከመስጠት፣ በትምህርት አቀባበላቸው ደከም ያሉትን ማበረታታት አይሻልም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ትምህርት ቢሮው በበኩሉ የቅዳሜው የማጠናከሪያ ትምህርት ለተመረጡት ተማሪዎች ብቻ ይሰጥ እንጂ ከሰኞ እስከ አርብ ባለው ጊዜ ውስጥ ከመደበኛ የትምህርት ሰዓት ውጪ ለሌሎቹም ትኩረት ተሰጥቷቸው እያጠኑ ነው ብሏል፡፡

የትምህርት ቢሮው ምክትል ስራ ኃላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ ጥሩ ውጤት ላላቸው ተማሪዎች ማጠናከሪያ ከመስጠት፣ በትምህርት አቀባበላቸው ደከም ያሉትን ማበረታታት አይሻልም ወይ? ለሚለው ጥያቄ ሲመልሱ ጎበዝ ተማሪዎችን የመረጥነው በሁለት ምክንያቶች ነው ብለዋል፡፡
አንደኛ በተማሪዎች መካከል ፉክክር ለመፍጠር ሲሆን ሌላው ደግሞ ማጠናከሪያውን የወሰዱ ተማሪዎች ሌሎችን እንዲያስጠኑ ነው ሲሉ ኃላፊው መልሰዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
ንጋት መኮንን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp https://tinyurl.com/ycxjmm3s








