top of page

''የኢራኑን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሀላፊ ዓሊ ላርጃኒን ገድለነዋል'' እስራኤል

  • 2 hours ago
  • 1 min read

መጋቢት 8/2018


የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ የኢራኑን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሀላፊ ዓሊ ላርጃኒን ገድለነዋል አሉ፡፡


ካትዝ እንደተናገሩት ላርጃኒ የተገደሉት እስራኤል ትናንት ለዛሬ አጥቢያ ኢራን ውስጥ በፈፀመችው ድብደባ ነው፡፡

ዓሊ ላርጃኒ ከሁለት ሳምንታት በፊት በአሜሪካ እና በእስራኤል ጣምራ ጥቃት የተገደሉትን የቀድሞውን ጠቅላይ መሪ አያቶላ ዓሊ ሐሚኒን ለመተካት በእጩነት ከቀረቡት አንዱ ነበሩ፡፡


አባታቸውን በመወከል በጠቅላይ መሪነት የተመረጡት ሞጅታባ ሐሚኒ መሆናቸው ይታወቃል፡፡


ዓሊ ላርጃኒ በእስራኤል ጥቃት ተገድለዋል ስለመባሉ እስካሁን ከኢራን በኩል ማረጋገጫም ይሁን ማስተባበያ እንዳልተሰጠ ሬውተርስ ፅፏል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page