top of page

የትግራዩን ጦርነት ያስቆመውን ስምምነት የተፈራረሙ ወገኖች ፖለቲካዊ ምክክር እንዲያደርጉ የአውሮፓ ህብረት ልዑክ ጠየቀ

  • sheger1021fm
  • 1 day ago
  • 1 min read

ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም


የትግራዩን ጦርነት ያስቆመውን የሰላም ስምምነት የተፈራረሙ ወገኖች ከመጪው ምርጫ በፊት ፖለቲካዊ ምክክር እንዲያደርጉ በኢትዮጵያ የሚገኘው የአውሮፓ ህብረት ልዑክ ጠየቀ፡፡


የህብረቱ ልዑክ ከተፈረመ ትላንት 3 ዓመት የሞላውን የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምት አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡


በመግለጫውም የፕሪቶሪያው የሠላም ስምምነት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እንዲደረግ እና የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀዬቸው እንዲመለሱ አሳስቧል።


ጦርነት መቆሙን እና የተቋረጡ መንግስታዊ አገልግሎቶች እንዲቀጥሉ መደረጋቸው እንደ በጎ እርምጃ የሚወሰዱ ናቸው ያለው መግለጫው ቀሪ የስምምነቱ ክፍሎችም ተፈጻሚ እንዲሆኑ ጠይቋል።


የተጀመረው የትጥቅ ማስፈታት እና ማስረከብ እንዲቀጥል እንዲሁም ታጣቂዎች ሠላማዊ ህይወት የሚመሩበት አሰራር እንዲቀጥል ፍላጎታችን ነው ብሏል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page