top of page

የቤት ሰራተኞችን በተመለከተ ግልፅ የሆነ ህግ ባለመበጀቱ  የሚደርስባቸዉን ጥቃት ለመከላከልና  መብታቸዉን ለማስከበር አስቸጋሪ እንዳደረገዉም አንድ ጥናት አመላከተ።

  • Feb 26
  • 1 min read

የካቲት 19/2018  

 

የቤት ሰራተኞችን በተመለከተ ግልፅ የሆነ ህግ ባለመበጀቱ  የሚደርስባቸዉን ጥቃት ለመከላከልና  መብታቸዉን ለማስከበር አስቸጋሪ እንዳደረገዉም አንድ ጥናት አመላከተ።

 

 ዕድሜያቸው ከ10 ዓመት በታችየሆኑ ህፃናት በቤት ሰራተኝነትተሰማርተው እንደሚገኙ በጥናቱ ተጠቁሟል።

 

አባዛኛዉን “ከገጠሪቱየሀገራችን ክፍሎችየተሻለ ህይወትን ፍለጋ ወደከተማ በመሰደድ በሰውቤት ተቀጥረው የቤቱን ስራ የሚከዉኑ፣ ልጆችን የሚሳድጉ፣ማዕድ የሚያዘጋጁ የቤት ሴት ሰራተኞች የተለያየጥቃት እንደሚደርስባቸዉም በጥናቱ ተጠቁሟል።



ፎረም ፎርሶሻል ስተዲስ (FSS)የተባለው መንግስታዊ ልሆነ  የጥናትተቋም  ከ2015 እስከ 2016 ዓ.ም አካሄደኩት ባለዉና ሰሞኑን ይፋ ባደረገዉ ጥናት፣ በሴት የቤትሰራተኞች ላይ ስነ ልቦናዊ እና ቃላዊ ጥቃት እንደሚደርስባቸዉ  በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሶሽዮሎጅና የሶሻል አንትሮፖሎጅ መምህር የሆኑት ሰላም ኢሳያስ( ዶ/ር ) ነግረውናል።

 

በጥናቱ ከተካተቱት ሰራተኞች መካከል አብዛኛዎቹ ከገጠር አካባቢ የመጡ ሲሆኑ፣ ተቀጥረዉ በሚሰሩባቸዉ ቤቶች አስከ 18 ሰዓት በስራ እንደማሳልፉም ተጠቁሟል። 

 

እነዚህ ህፃናት ለትምህረትና የተሻለ ህይወት እንዲኖሩ በሚል ሰበብ በቅርብ ዘመድ ፣በአክስት፣ በአጎት፣ በወዳጅና በጓደኛ ወደ ከተማ ከተወሰዱ በኋላ የቤት ሰራተኛ ሆነዉ ከባባድ ስራዎችን እንደሚያከናዉኑ በጥናቱ መገኘቱ ተመላክቷል።

 

አብዛኛዉ የቤት ሰራተኞች ያለ እድሚያቸዉ የተወለዱበትን ቀዬ ለቀዉ፣ ከቤተሰብ ተነጥለዉ  በዚህ የስራ ዘርፍ እንዲገቡ ከሚያደርጓቸዉ ዉስጥ ድህነት፣ ያለ እድሜ መዉለድ፣ ያለድሜ ጋብቻንን ሽሽትና ሌሎችም  እንደሚገኙበት ጥናቱ ተጠቁሟል። 

 

ይህንን ችግር  ለማስቆም በአስቸኳይ ህግ ተበጅቶለት ደንብ  ወጥቶለት ህግ አስፈፃሚዎች ሌሎች ይመለከተኛል የሚሉ ሁሉ  በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተመላክቷል።

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

 

ገዛ ጌታሁን

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

 

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page