የሚበዙት ባንኮች ከመደበኛ ስራቸው ውጪ በሆኑ ሌሎች ተግባራት መሰማራታቸው
- sheger1021fm
- 22 minutes ago
- 1 min read
ህዳር 4 2018
የባንኮች በአቅምም፣ በአገልግሎት ጥራትም ልቀው የመገኘት ሀሳብ በየጊዜው ይነሳል።
ባንኮች ወደፊት ለሚመጣው ፉክክር ዝግጁ መሆን አለባቸው ይባላል።
በሌላ በኩል የሚበዙት ባንኮች ከመደበኛ ስራቸው ውጪ በሆኑ ሌሎች ተግባራት ሲሰማሩ ይታያል።
በኢ-ኮሜርስ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በሎጅስቲክስና በሌላው መፎካከራቸው በዝቶ እየታየ ነው።

የክፍያ ሥርዓትን ማገዝ የሚጠበቅባቸው ባንኮች፣ ሶፍትዌር አበልፅገው በተለያየ ንግድና አገልግሎት ውስጥ ሲሳተፉ ይታያል።
ይህም የተቋቋሙበት ዓላማ ይህ ነው ወይ? የሚል ጥያቄን ያስነሳል።
ባንኮች ከድንችና ሽንኩርት ሽያጭ እስከ ሎጅስቲክ ዘርፍ ገብተው ሲሰሩ ይታያል፡፡
የባንክ ስራውን ከማሳደግና ማቀላጠፍ ወደዚህ ዓይነት ስራ ውስጥ መግባታቸው ምን ይዞ ይመጣል? ባለሙያ ጠይቀናል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s








