top of page

የ1997 እና የ2005 ዓ.ም የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚቆጥቡ የማህበረሰብ ክፍሎች

  • sheger1021fm
  • 21 minutes ago
  • 1 min read

ታህሳስ 16/2018 

 

የጋራ መኖሪያ ቤት ለማግኘት ተመዝግበው የሚጠባበቁ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሉ፡፡

 

እጣ ፈንታችን ምንድነው? ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡

 

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በበኩሉ በተለያየ መልኩ እየተተገበሩ ባሉ ፕሮግራሞች ቤት የማግኘት እድል አላቸው ብሏል፡፡

 

እነዚህ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚቆጥቡ የማህበረሰብ ክፍሎች የ1997 እና የ2005 ዓ.ም መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

 

በዚህ ጉዳይ ከዚህ ቀደም የሚመለከታቸው የሚባሉ የስራ ሀላፊዎችን መጠየቃቸውና መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉም ያስረዳሉ፡፡

 

ነዋሪዎቹ ቁጠባቸውን እንዳላቋረጡ እና አሁን የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር እያስገነባ ከሚገኘው ቤት የማግኘት እድል ይኖረናል ወይ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

 

ree

በአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አብዲሳ አራርሶ የ1997 እና የ2005 ዓ.ም የቤት ቆጣቢዎችን በአስራ አራተኛው ዙር የመጨረሻው ዕጣ ሲወጣ እንደ የቤት ፍላጎታቸው ሙሉ የቆጠቡትን አዳርሰናል ማለት ይቻላል ሲሉ መልሰዋል፡፡

 

ሆኖም ቀረን የሚሉ ካሉ አሁንም ቤት የማግኘት እድል አላቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..

 

ማርታ በቀለ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

  

  

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page