top of page

የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ሙሉ ለሙሉ ለመስጠት የግብዓት እጥረት እንደገጠማቸው ያነጋገርናቸው ክልሎች ተናገሩ፡፡

  • 12 minutes ago
  • 1 min read

ግንቦት 20/2018


የ12ኛ ክፍል ፈተናን በኦንላይን ሙሉ ለሙሉ ለመስጠት የግብዓት እጥረት እንደገጠማቸው ያነጋገርናቸው ክልሎች ተናገሩ፡፡


ከሰኔ 24 ጀምሮ የሚሰጠው የ12ተኛ ክፍል ፈተና ሙሉ ለሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ትምህርት ሚኒስቴር ዝግጅት ማጠናቀቁን በተለያዩ ጊዜያት መነገሩ ይታወሳል፡፡


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በክልሉ ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል በኦንላይን መፈተን የሚችለው 76 በመቶ ብቻ መሆኑን አስረድቷል፡፡


በቀሪ ጊዜ ይህንን ቁጥር ወደ 80 በመቶ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን ቢሮው የጠቀሰ ሲሆን ዘንድሮ 24 በመቶ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን በወረቀት ለመፈተን እየተዘጋጀ መሆኑን ነግሮናል፡፡


ለፈተናው የሚያስፈልጉ የኮምፒዩተር እጥረት፣ የኢንተርኔት አለመሟላት እና ሌሎች ግብአቶች እጥረት ማጋጠሙ ተሰምቷል፡፡


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ በበኩሉ ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል 65 ከመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ብቻ በኦንላይን ይፈተናሉ ብሏል፡፡


ቀሪውዎቹ በወረቀት እንደሚፈተኑ የተነገረ ሲሆን በኦንላይን የሚፈተኑ ተማሪዎች ሰሞኑን የሙከራ ፈተና እየወሰዱ ነው ተብሏል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ.......



በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…










Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page