የምግብ ችግር እያለባትም፤ ካመረተችው ግማሽ የሚጠጋውን የምትደፋዋ ኢትዮጵያ!
- 6 hours ago
- 1 min read
ግንቦት 20/2018
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ገበሬው ከሚያመርተው ምርት ከ40 በመቶ በላዩ ከገበታ ሳይደርስ ባክኖ ይቀራል።
በየዓመቱ ከሚመረት እንደ ሽንኩርትና ቲማቲም ያለው ቶሎ የሚበላሽ የግብርና ምርት ግማሽ ያክሉ ተበላሽቶ የሚደፋ እንደሆነ ይነገራል።
አፍሪካ በዚህ መንገድ ገበሬዎቿ ቢያመርቱም 4 ቢሊየን ዶላር የሚገመት ምርት ተበላሽቶ መልሳ ትደፋለች።
ከዚህ ጀርባ ያለው ትልቁ ችግር የቀዝቃዛ ምርት ማጓጓዣና መስቀመጫ ሰንሰለት አለመኖር ነው ይባላል።

ያደጉት ሀገሮች ከአጠቃላይ ምርታቸው የምርት ብክነትን ከ1 በመቶ በታች ማውረድ ችለዋል።
ኢትዮጵያ ግን የምግብ ችግር ቢኖርባትም፤ ዛሬም ብዙ ስለማምረት ብትደክምም ካመረተችው ግማሽ ያክሉን እየደፋች ቀጥላለች።
ታዲያ ምን ይበጃል? የቀዝቃዛ ምርት ሰንሰለትን ማስፋፋትስ ለምን ከባድ ሆነ?
የዘርፉ ባለሙያዎች ብዙ ስለማምረት ብቻ ሳይሆን ብክነትን ስለመቀነስም መጨነቅ ይገባል ይላሉ።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ……
ቴዎድሮስ ወርቁ





Comments