top of page

ዘንድሮ በሚካሄደው ሰባተኛ ሀገራዊ ምርጫ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሻለ ድምፅ በፓርላማው እንዲኖራቸው እንደሚፈልጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።

  • sheger1021fm
  • 7 minutes ago
  • 1 min read

ጥር 26/2018

 

ዘንድሮ በሚካሄደው ሰባተኛ ሀገራዊ ምርጫ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የተሻለ ድምፅ በፓርላማው እንዲኖራቸው እንደሚፈልጉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ።

 

መንግስት ስራውን ትቶ በምርጫ ስራ ላይ አተኩሯል በሚል ለቀረበው ጥያቄ ጠቅላይ ሚንስትሩ ሲመልሱ ብልፅግና ፓርቲ ምርጫው ላይ አተኩራችሁ እየሰራችሁ አይደለም ዋና ትኩረታችን በመንግስት ስራ ላይ ነው እያሉን ነው ብለዋል።

 

ከምርጫ ቅስቀሳ ጋር በተያያዘ ወጣቱን ለመድረስ አሁን ያሉ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም የተሻለ ነው የህዝብ መገናኛ ብዙሃን ለሁሉም እኩል ተደራሽ እንዲሆን እንሰራለን ብለዋል ጠቅላይ ሚንስትሩ።

 

ከፀጥታ ጋር በተያያዘ ለምርጫው ስጋት ነው ተብሎ ለተነሳው ጥያቄ ሲመልሱ ባለፉት 6 ወራት በተደረጉ የአደባባይ በዓላት ምንም ችግር ሳይፈጠር ተጠናቋል ታዲያ ምርጫው ሲደረግ እንዴት የፀጥታ ስጋት ይሆናል ሲሉም ጠይቀዋል።

 

መንግስት ምርጫውን ለማድረግ ዝግጁ ነው በምርጫው የተፎካካሪ ፓርቲዎች የድምፅ ተሳትፎ ከባለፈው የተሻለ እንዲሆን ነው እየሰራን ያለነው ብለዋል።

 

በሀገራዊ ምክክር ማንም እንዲሳተፍ ነው የተፈቀደው ፍላጎት የሌለውን ቡድን ግን ማስገደድ አይቻልም ሲሉም ተናግረዋል።

 

የኮሚሽኑ ቀጣይ ስራ ተወያዮችን አወያይቶ ለመንግስትና ለምክርቤቱ ምክረ ሀሳብ ማቅረብ ነው ተብሏል።

 

በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

 

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page