ዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብቴ ከ100 ቢሊዮን ብር አለፈ አለ፡፡
- sheger1021fm
- 18 hours ago
- 1 min read
ጥር 19/2018
ዘመን ባንክ አጠቃላይ ሀብቴ ከ100 ቢሊዮን ብር አለፈ አለ፡፡
የተከፈለ ካፒታሉም14 ቢሊዮን ብር መድረሱን በላከልን መግለጫ ላይ ጠቅሷል፡፡
ባንኩ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ አጠቃላይ ሀብት 106 ቢሊዮን ብር፣ ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ 80 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተናግሯል፡፡
ይህም ባንኩ የተረጋጋ ዕድገትና ጠንካራ የደንበኞች አመኔታ እንዳለው የሚያሳይ ነው ሲሉ የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደረጀ ዘበነ አስረድተዋል፡፡

ዘመን ባንክ በዚህ ጊዜ ውስጥ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡም ተጠቅሷል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው የባንኩ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ስኬት ካለፈው ዓመት ከነበረው የሥራ አፈፃፀም ጋር ሲወዳደር የዘንድሮው የላቀና ስኬታማ የሥራ ጊዜ ያሳለፍንበት ነበር ሲሉ አስረድተዋል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://url-shortener.me/2DUB
Instagram: https://url-shortener.me/2DUD












Comments