በተመድ በአለም አቀፍ ደረጃ 2026 የአርብቶ አደር እና የግጦሽ መሬት ዓመት እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ መደረጉ ተሰማ
- sheger1021fm
- 16 hours ago
- 1 min read
ጥር 19/2018
የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እና የአየር ጠባይ ለውጥንም ለመቋቋም ይረዳል ተብሎ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአለም አቀፍ ደረጃ 2026 የአርብቶ አደር እና የግጦሽ መሬት ዓመት እንዲሆን በተወሰነው መሰረት አዲስ አበባ ላይ ጉባኤ መደረጉ ተሰማ፡፡
ከግብርና ሚኒስቴር ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰላም እና ፀጥታ ኢንስቲትዩ ጋር በመተባበር የመንግስታቱ ድርጅት በወሰነው መሰረት በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ ምሁራንና የአርብቶ አደሮች መወያየታቸው ተሰምቷል፡፡
በኢትዮጵያ ከ12 እስከ 15 በመቶ የሚደርሱ የማህበረሰብ አባላት አርብቶ አደር መሆናቸው የሚነገር ሲሆን ኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ድርሻ አላቸውም ተብሏል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ከ300 ሚሊዮን በላይ አርብቶ አደሮች መኖራቸው የሚናገሩት የፓስቶራሊስት ፎረም ኢትዮጵያ ዳይሬክተር ተዘራ ጌታሁን ዋናው ትኩረቱ የአየር ጠባይ ለውጥ ችግርን መከላከልና በምግብ እህል እራስን ለመቻል ለሚደረገው ትግል የአርብቶ አደር የእንስሳትና የግጦሽ መሬት ጉዳይ ቀዳሚው ነው ብለዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
የኔነህ ሲሳይ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7












Comments