top of page

ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ለመጀመር እስካሁን ያደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • Nov 17
  • 2 min read

ህዳር 8 2018


ወደ ትግራይ ክልል ገብቶ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ለመጀመር እስካሁን ያደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት እንዳላመጣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡


ኮሚሽኑ ይህንን ያለው ካሳለፍነው ህዳር 5 እስከ 7 2018 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር በመከተበት ወቅት ነው፡፡


የተሳታፊ ልየታና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎችን በማገባደድ ወደ ሃገራዊ ምክክር ጉዳኤው ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ስራዎች እየከወነ መሆኑን የሚናገረው ኮሚሽኑ በሂደቱ የገጠሙትን ፈተናዎችም ጠቅሷል፡፡


ከችግሮቹ መካከል ቀዳሚው ነው ያለው እስካሁን ድረስ በትግራይ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ ስራዎች አለመጀመራቸውን ነው፡፡

ree

የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር መላኩ ወልደማሪያም ስለዚህ ሲያስረዱ ኮሚሽኑ ከፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረም ማግስት ጀምሮ በትግራይ ክልል እንዴት ስራው ይሰራ በሚለው ጉዳይ ዙሪያ፤ ከህወሃት አመራሮችንና ከሌሎችም ባለድርሻዎች በተደጋጋሚ መነጋገር ችሏል ብለዋል፡፡


ይሁንና በውይይቶቹ ከህውሃት ወገን ከፕሪቶሪያው ስምምነት አተገባበር ጋር  የተያያዙ ጥያቄዎች ተነስተውልናል ያሉት ኮሚሽነር መላኩ ጥያቄዎቹ የፌድራል መንግስቱን የሚመለከቱ በመሆኑ ለመንግስት አቅርበን ምላሽም እንዲያገኙ ግፊት እያደረግን ነው፤ እስካሁን ችግሮቹ ባለመፈታታቸው በተያዘው እቅድ መሰረት ወደ ትግራይ ገብተን አጀንዳ ማሰባሰብ አልቻልንም ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ሌላውና ኮሚሽኑ በስራው ሂደት ገጠመኝ ያለው ችግር የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሟላ መልኩ አለመሳተፍ ነው፡፡

ree

በሂደቱ በኢትዮጵያ ካሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች 80 በመቶዎቹ ከኮሚሽኑ ጋር እየሰሩ ቢሆንም ሂደቱን አቋርጠው የወጡ ፓርቲዎችን ለማካተት ፅህፈት ቤቱ ድረስ በመጥራት እያነጋገረ ነው ተብሏል፡፡


ፓርቲዎቹ ምክክሩን ለቅቀው ለመውጣቻቸው የሚያነሱት ምክንያት ፖለቲካዊ ነው፤ጥያቄያቸው ከመንግስት ጋር የተገናኘ ነው ብለዋል ኮሚሽነሩ፡፡


ኮሚሽኑ የገጠሙት ችግሮች ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው በመሆኑ ፖለቲካዊ ውሳኔ የሚፈልጉ ናቸው ያሉት ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ ናቸው፡፡


እስካሁን በምክክር ሂደቱ ያልተሳተፉ የታጠቁ ቡድኖችንና የፓለቲካ ፓርቲዎችን ለማሳተፍ የሚያደርገውን ጥረት እንደሚቀጥል ያነሱት ዋና ኮሚሽነሩ በዚህ ዓመት ሃገራዊ ምክክሩንና ሃገራዊ ምርጫውን አጣጥሞ ማስኬድ ያስፈልጋልም ብለዋል፡፡


የአጀንዳ ቀረፃ ስራውን በማጠናቀቅ ምክክር የሚደረግባቸውን አጀንዳዎች ይፋ ለማድረግ እየሰራ ነው መሆኑንም የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሲናገር ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

ምንታምር ፀጋው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page